መስከረም 08 ቀን 2019ዓ.ም.(መናኸሪያ ሬዲዮ) የማንቸስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ እሁድ ዕለት በኦልድ ትራፎርድ ማንቸስተር ዩናይትድን 1-0 ባሸነፉበት የደርቢ ጨዋታ ላይ በኤርሊንግ ሀላንድ ብቸኛ ጎል ታግዘው 199ኛውን የማንቹሪያን ደርቢ በድል መወጣታቸው የሚታወስ ነው። ታዲያ በጎሉ ዙሪያ የተነሳውን የVAR ውዝግብ አስመልክተው የሰጡት ምላሽ የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን ትኩረት ስቧል። የዳኞች የበላይ አካል PGMOL በጨዋታው ወቅት የVAR ዳኞች ኤንዞ ፈርናንዴዝ በኦፍሳይድ ስፍራ ሆኖ እንቅስቃሴ በማድረጉ የሀላንድ ግብ መሻር ነበረበት በማለት ለዩናይትድ ይቅርታ መጠየቃቸውን ተከትሎ፣ ማሬስካ ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ጠንካራ አስተያየት ሰጥተዋል። ማሬስካ በ2023 በኦልድ ትራፎርድ ሲቲ 2-1 በተረታበት ጨዋታ ማርከስ ራሽፎርድ በግልጽ ኦፍሳይድ ላይ ሆኖ ኳሱን ሳይነካ በመሮጡ የብሩኖ ፈርናንዴዝ ግብ መጽደቁን በማስታወስ ነው “እኛም ከሶስት ዓመት በፊት ለተቆጠረብን መደበኛ ያልሆነ ግብ እስከዛሬ የPGMOLን ይቅርታ እየጠበቅን ነው” ሲሉ ምላሽ የሰጡት ኤንዞ ማሬስካ በጊዜው አሰልጣኝየነበሩት የአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ምክትል በመሆን ይሰራ እንደነበር ይታወቃል። በተጨማሪም ማሬስካ ቡድናቸው ፊል ፎደን በ23ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከወጣበት በኋላ ለ70 ደቂቃዎች ያህል በ10 ተጫዋች ተከላክሎ እና ተፋልሞ ያመጣውን አስደናቂ ድል ትቶ፣ ትኩረቱን በሙሉ በአንድ የVAR ውሳኔ ላይ ማድረግ “ደካማ አመለካከት” ነው ሲሉ ተናግረዋል። በኳስ ጨዋታ የውሳኔ ስህተቶች አንዳንዴ ወደ አንተ አንዳንዴ ደግሞ በተቃራኒ ቡድን ጸጋ ይዘው ሊመጡ እንደሚችሉና ዳኞች በሰከንዶች ውስጥ ውሳኔ መስጠት ስላለባቸው ስህተት ተፈጥሯዊ መሆኑን አክለው ገልጸዋል። ማንቸስተር ሲቲ አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካን የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ከሾመ በኋላ በዚህ የውድድር ዘመን አስደናቂ ጅማሮን በማሳየት ሁሉንም ጨዋታዎች በድል በመወጣት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን በጎል ክፍያ እየመራ ይገኛል። የማንቸስተር ሲቲው አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ አያይዘው በኮሚኒቲ ሺልድ ጨዋታ ወቅት ባጋጠመው የባት ጉዳት ምክንያት ከሜዳ ርቆ የቆየው የ24 ዓመቱ ቤልጂየማዊ የክንፍ አጥቂ ዠሬሚ ዶኩ (Jeremy Doku) ወደ ሙሉ አካላዊ ብቃት ተመልሶ ለጨዋታ ዝግጁ ለመሆን በጣም መቃረቡን ተናግረዋል። አሰልጣኝ ማሬስካ ስለ ተጫዋቹ አጠቃላይ ሁኔታ ሲናገሩ “ዶኩ ወደ ስብስቡ ለመመለስ በጣም ተቃርቧል፤ በዚህም ደስተኞች ነን፤ ተጫዋቹ ለቡድናችን ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያለው ተጫዋች ነው” ሲሉ ገልጸውታል። ___ ሀሳብ እና‘ሳ‘ፍራለን
Related Posts
ፊዮሬንቲና ጆሹዋ ዚርክዚን ለማስፈረም የዝውውር ጥያቄ ማቅረቡ ተገለጸ
ነሐሴ 22 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የጣሊያኑ ክለብ ፊዮሬንቲና የ25 ዓመቱን የማንቸስተር ዩናይትድ እና የኔዘርላንድስ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ ጆሹዋ ዚርክዚን ለማስፈረም... read more
ማንቸስተር ሲቲዎች ፍሎሪያን ቪርትዝን ለማስፈረም ከሚደረገው ፉክክር ራሳቸውን አገለሉ
የ22 አመቱ ጀርመናዊ የአጥቂ አማካኝ መስመር ተጫዋች በአሁን ሰአት ከሚፈለጉ ፤ በጣም አስደናቂ እንቅስቃሴን ከሚያደርጉ ተጫዋቾች ተርታ ስሙ ይሰለፋል።
ታዲያ ተጫዋቹን... read more
ሊቨርፑል ሚሎሽ ኬርኬዝን ሁለተኛ ፈራሚያቸው ለማድረግ ተቃርበዋል
ይሄ ሀንጋሪአዊ በ2023 ሰኔ ወር ላይ በርንማውዝን ከተቀላቀለ በኋላ በጣም አስደናቂ የግል አቅሙን እያስመለከተ ይገኛል። በዛ ላይ ገና 20 አመቱ... read more
በክለቦች ትልቁ የውድድር መድረክ በሆነው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ እጅግ በጣም ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ነው ተብሏል
👉ተጠባቂ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታን ይዞ በዛሬው እለት ኤምሬትስ ስቴዲየም ላይ ይመለሳል
አርሰናልን ከ ፓሪስ ሴንት ጄርሜ ጋር የሚያገናኘው ይህ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ... read more
ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ እስከ 2029 የማድሪድ ፕሬዚዳንት ሆነው እንደሚቀጥሉ ታወቀ
ስኬታማ የቢዝነስ ሰው እና የክለብ ፕሬዚዳንት እንደሆኑ የሚነገርላቸው ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ ሮድሪጌዝ ለተጨማሪ 4 አመት የማድሪድ ፕሬዚዳንት ሆነው እንደሚያገለግሉ በፊርማቸው አረጋግጠዋል።
ለፉክክር... read more
የሻምፒዮንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ዳሰሳ
በየአመቱ ከሚከናወኑ እና የክለቦች ፉክክር ከሚደምቅበት እንዲሁም በአውሮፓ ውስጥ ሀያሉ ክለብ ለመባል የሚደረግ የክለቦች ትንቅንቅ በተለያዩ የአውሮፓ ግዙፍ ስቴዲየሞች በባውዛ... read more
አርሰናል በሪዮ ንጎሞሀ ላይ የቅርብ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ የሚጠቁሙ መረጃዎች ወጥተዋል
መስከረም 05 ቀን 2019ዓ.ም.(መናኸሪያ ሬዲዮ) የቲምቶክ ጸሐፊ ጋዜጠኛ አለን ኒክሰን እንዲሁም ሪለክተንት ኒኮ ያወጡት መረጃ፣ መድፈኞቹ ይህንን ተስፈኛ ወጣት ኮከብ... read more
የሳዑዲ ፕሮ ሊግ ክለብ አልሂላል የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ ኦሊ ዋትኪንስን ከአስቶን ቪላ ለማስፈረም ከስምምነት ላይ መድረሱ ተሰማ።
ነሐሴ 22 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የዝውውር ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራው ታዋቂው ጋዜጠኛ ፋብሪዚዮ ሮማኖ እንደገለጸው፣ ሁለቱ ክለቦች በ58.4 ሚሊዮን... read more
ማንቸስተር ሲቲዎች ኢሊማን ንዲያዬን ለማስፈረም ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተገለጸ
ነሐሴ 23 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ማንቸስተር ሲቲዎች የዝውውር መስኮቱ ከመዘጋቱ በፊት የኤቨርተኑን ኢሊማን ንዲያዬን ለማስፈረም ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ጋዜጠኛ ቤን... read more
UFC የፍልሚያ ምሽት በለንደን ተከናውኗል
የአለማችን ትልቁ የፍልሚያ መድረክ የሆነው እና የሚክስድ ማርሻል አርት ክህሎት ያላቸው ተፋላሚዎች በየክብደት እርከናቸው ተከፋፍለው በሚያከናውኑት የፍልሚያ መድረክ ትላንት በእንግሊዝ... read more
ምላሽ ይስጡ