ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፥ የቀድሞዋን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን በምስራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ተፅዕኖን እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን በበላይነት የማጠናከር እና የማስተካከል ትልቅ ኃላፊነት እንደሰጧቸው ተሰማ። ይህ የተሰጣቸው አዲስ ተልዕኮ በቀጠናው እየታዩ ያሉ የጸጥታ እና የዲፕሎማሲ መሻከር አዝማሚያዎችን በታዋቂ እና አንጋፋ ዲፕሎማቶች አማካኝነት ለመፍታት ከተያዘው የድርጅቱ ስትራቴጂ ጋር የተያያዘ መሆኑ ታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውስጥ ምንጮች እንደገለጹት፣ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በቀጠናው ባላቸው የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲ ልምድ፣ በተለይም ቀደም ሲል በጅቡቲ፣ በሴኔጋል እና በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (IGAD) እና በአፍሪካ ህብረት የዩኤን ልዩ መልዕክተኛ ሆነው በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ የሰሩ በመሆናቸው ለዚህ ታላቅ ቀጠናዊ ሚና ተመራጭ አድርጓቸዋል።
ዋና ፀሐፊው አንቶኒዮ ጉተሬዝ ይህንን ውሳኔ ያሳለፉት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ለማርገብ፣ በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር መልሶ ለመገንባት እና የድርጅቱን ቀጠናዊ ተሰሚነት ከፍ ለማድረግ ታስቦ መሆኑ ተጠቁሟል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴም በቅርቡ የስልጣን ዘመናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በተለያዩ አህጉራዊ የግጭት አፈታት እና የሰላም ግንባታ ውይይቶች ላይ በንቃት እየተሳተፉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ይህ ሹመት ዩኤን ለአፍሪካ ቀንድ ቀውስ ዘላቂ መፍትሄ ለመፈለግ በወሰደው ስልታዊ እርምጃ ውስጥ ትልቅ ግምት የተሰጠው ሲሆን፥ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እና የሹመቱን ሙሉ ይዘት እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ትራምፕ ለሪፐብሊካኖች ማስጠንቀቂያ ሰጡ
👉'እብድ አትሁኑ! 'ሲሉ ገልጸዋል
ሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሪፐብሊካኖች ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል፤ ይህም ሴኔት "ትልቅ እና ቆንጆ... read more
ጡረታ የወጡ አረጋውያን ተደራጅተው በሙያቸው አመቺ በሆነ የስራ መስክ እንዲሰማሩ ለማድረግ የሚያስችል መመሪያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ
ኅዳር 19 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) እድሜያቸው ከ60 አመት በላይ የሆኑና ጡረታ የወጡ ነገር ግን የመስራት አቅም ያላቸው አረጋውያን በሙያቸው ተሰማርተው... read more
ውስጣዊ የሰላም ችግር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች መቀያየር የዲፕሎማሲው ዘርፍ ተግዳሮቶች እንደነበሩ ተገለጸ
ኅዳር 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ባለፉት 5 ዓመታት ሀገር ውስጥ ያሉ ግጨቶችና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች መቀያየር ተቋሙ ውጤታማ እንዳይሆን እንዳደረገው... read more
በሰራተኞች አድማ ምክንያት አየር መንገዱ በረራዎቹን ለጊዜው አቋረጠ
ነሐሴ 12 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) የካናዳ አየር መንገድ(Air Canada)በአድማ ላይ ያሉ የበረራ አስተናጋጆች ወደ ስራ እንዲመለሱ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ባለመቀበላቸው... read more
ኢትዮጵያ የፕላስቲክ ምርት ማምረት ካቆመች እስከ 50 ቢሊየን ብር በዓመት እንደምታጣ ተጠቆመ
ሰኔ 13 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ለአካባቢ ብክለት የሚዳርጉ እና አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ ምርቶች በሥነ ምህዳር ላይ የሚያደርሱትን ጉዳት... read more
ቆዳን እስከ አጥንት የማራገፍ ምትሀታዊ ችሎታ ያለው የነብር ምላስ
ሐምሌ 12 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በዓለም የዱር እንስሳት ስነ-ምህዳር ውስጥ የላቀ ቦታ የሚሰጠውና በአድኖ ችሎታው የሚታወቀው ነብር፣ በቀላሉ የሚታይ ነገር... read more
መሉጌታ ከበደን (ወሎዬው) የሚዘክር ኮሚቴ ተቋቋመ
ሐምሌ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የቀድሞ የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአጥቂ መስመር ተጫዋች የሆነው ሙሉጌታ ከበደን የሚዘክር ኮሚቴ በዛሬው... read more
ራሱን “የቅማንት ታጣቂ ቡድን” ብሎ የሚጠራው ኀይል የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ለመቀበል ስምምነት ላይ መድረሱ ተገለጸ
ኅዳር 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በምዕራብ ጎንደር መተማ ወረዳ መቃ ቀበሌ ከሚንቀሳቀሱ የታጣቂ ተወካዮች ጋር ውይይት መካሄዱ ተገለጸ፡፡ በውይይቱ በመቃ... read more
ከቅመማ ቅመም ምርት ከ3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ ተገለጸ
ታኅሳስ 02 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ከቅመማ ቅመም ምርት የወጪ ንግድ ለማግኘት ከታቀደው እቅድ ከ75 በመቶ በላይ ማሳካት እንደታቻለ የኢትዮጵያ ቡና እና... read more
በማይናማር የሚገኙ ዜጎችን ማስመለሱ ቢቀጥልም አሁንም በህገ ወጥ መንገድ ወደ ስፍራው የሚያቀኑ ዜጎች መበራከታቸው ተገልጿል
በማይናማር የሚገኙ ዜጎችን ማስመለሱ ቢቀጥልም አሁንም በህገ ወጥ መንገድ ወደ ስፍራው የሚያቀኑ ዜጎች መበራከታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ... read more
ምላሽ ይስጡ