ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፥ የቀድሞዋን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን በምስራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ተፅዕኖን እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን በበላይነት የማጠናከር እና የማስተካከል ትልቅ ኃላፊነት እንደሰጧቸው ተሰማ። ይህ የተሰጣቸው አዲስ ተልዕኮ በቀጠናው እየታዩ ያሉ የጸጥታ እና የዲፕሎማሲ መሻከር አዝማሚያዎችን በታዋቂ እና አንጋፋ ዲፕሎማቶች አማካኝነት ለመፍታት ከተያዘው የድርጅቱ ስትራቴጂ ጋር የተያያዘ መሆኑ ታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውስጥ ምንጮች እንደገለጹት፣ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በቀጠናው ባላቸው የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲ ልምድ፣ በተለይም ቀደም ሲል በጅቡቲ፣ በሴኔጋል እና በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (IGAD) እና በአፍሪካ ህብረት የዩኤን ልዩ መልዕክተኛ ሆነው በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ የሰሩ በመሆናቸው ለዚህ ታላቅ ቀጠናዊ ሚና ተመራጭ አድርጓቸዋል።
ዋና ፀሐፊው አንቶኒዮ ጉተሬዝ ይህንን ውሳኔ ያሳለፉት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ለማርገብ፣ በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር መልሶ ለመገንባት እና የድርጅቱን ቀጠናዊ ተሰሚነት ከፍ ለማድረግ ታስቦ መሆኑ ተጠቁሟል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴም በቅርቡ የስልጣን ዘመናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በተለያዩ አህጉራዊ የግጭት አፈታት እና የሰላም ግንባታ ውይይቶች ላይ በንቃት እየተሳተፉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ይህ ሹመት ዩኤን ለአፍሪካ ቀንድ ቀውስ ዘላቂ መፍትሄ ለመፈለግ በወሰደው ስልታዊ እርምጃ ውስጥ ትልቅ ግምት የተሰጠው ሲሆን፥ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እና የሹመቱን ሙሉ ይዘት እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ለወራት በአየር ላይ የሚቆዩት “የሰማይ ላይ ሳተላይቶች”፦ የHALE ድሮኖች አዲስ አስገራሚ ስኬት!
ሚያዚያ 16 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአውሮፕላን ምህንድስናው ዘርፍ ከፍተኛ መነጋገሪያ የሆኑት High-altitude long-endurance (HALE) የተሰኙት ድሮኖች በከፍተኛ ከፍታ ላይ ለረጅም... read more
አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችው የባህር ላይ እገዳ እና የቻይና ጠንከር ያለ ምላሽ
ሚያዚያ 06 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)አሜሪካ ከኢራን ጋር ያደረገችው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ያለ ስምምነት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ በኢራን ወደቦች ላይ ጥብቅ የባህር ላይ... read more
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በተጨመረለት የ1 ዓመት የስራ ቆይታ አጀንዳዎችን የመቅረፅ እና ይፋ የማድረግ ስራ እንደሚሰራ ገለጸ
ሰሞኑን የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሦስት ዓመት የስራ... read more
በአለም አቀፍ ደረጃ እድሜን፣ ፆታን፣ የአኗኗር ሁኔታ እና ሌሎችንም ልዩነቶች ሳይመርጥ የዜጎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለው ተላላፊ ያልሆነ በሽታ
ሙሉ ፕሮግራሙን በድምጽ ለመስማት ከታች ያለውን ኦዲዮ ይጫኑ
በአለም አቀፍ ደረጃ እድሜን፣ ፆታን፣ የአኗኗር ሁኔታ እና ሌሎችንም ልዩነቶች ሳይመርጥ የዜጎችን ህይወት... read more
የታጁራ ወደብ ተጠቃሚነት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ በቅድሚያ ኢትዮጵያ የጀመረችዉን የወደብ ባለቤትነት የጥያቄ ሒደት መቋጨት አለባት ተባለ
ታኅሳስ 17 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ጅቡቲ በቅርቡ ኢትዮጵያ የታጁራ ወደብን መጠቀም እንደምትችል መግለጿ እና በኢትዮጵያ በኩል ግን ፍላጎት እንዳልተንጸባረቀ ማስታወቋ... read more
የምክክር ኮሚሽኑ ከምርጫው በፊት ሀገርን ያግባባ ይሆን?
የፖለቲካ ምህዳርን ማስፋትና ነጻ የሆነ ፖለቲካዊ ከባቢን መፍጠር ለዲሞክራሲና ለልማት ግንባታ አይነተኛ ቁልፍ ሚናን ይጫወታል በሚል ዛሬ ላይ የሰለጠኑ የምንላቸው... read more
መሉጌታ ከበደን (ወሎዬው) የሚዘክር ኮሚቴ ተቋቋመ
ሐምሌ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የቀድሞ የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአጥቂ መስመር ተጫዋች የሆነው ሙሉጌታ ከበደን የሚዘክር ኮሚቴ በዛሬው... read more
የከተማዋ ነዋሪዎች ግድቡ እስኪጠናቀቅ የሚያደርጉትን ድጋፍ እና የቦንድ ግዢ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ልዩ ህዝባዊ ንቅናቄ መጀመሩ ተገለጸ
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እስኪጠናቀቅ፣ የከተማዋ ነዋሪዎች የሚያደርጉትን ድጋፍ እና የቦንድ ግዢ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ልዩ ህዝባዊ ንቅናቄ መጀመሩን በአዲስ አበባ... read more
የወረቀት ተረፈ ምርቶችን በድጋሚ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ እየተሰራ ነው ተባለ
በተለያዩ አጋጣሚዎች ጥቅም የላቸውም ተብሎ የሚጣሉ ወረቀት እና ካርቶኖችን ለስራ እድል ፈጠራ እንዲውሉ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አንዲ ማማ ድርጅት አስታውቋል።... read more
በሀገሪቱ በነዳጅ የሚሰሩ ተሸከርካሪዎች ወደ ጋዝ ተጠቃሚነት ይቀየራሉ መባሉ ሀገሪቱ በከፍተኛ ድጎማ በምታስገባው የነዳጅ ምርት ላይ አንፃራዊ ለውጥ ያመጣል ተባለ
መስከረም 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ይህንን ያለው የኢትዮጵያ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማህበር ነው። ከሰሞኑ የኢፌደሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ... read more
ምላሽ ይስጡ