ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፥ የቀድሞዋን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን በምስራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ተፅዕኖን እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን በበላይነት የማጠናከር እና የማስተካከል ትልቅ ኃላፊነት እንደሰጧቸው ተሰማ። ይህ የተሰጣቸው አዲስ ተልዕኮ በቀጠናው እየታዩ ያሉ የጸጥታ እና የዲፕሎማሲ መሻከር አዝማሚያዎችን በታዋቂ እና አንጋፋ ዲፕሎማቶች አማካኝነት ለመፍታት ከተያዘው የድርጅቱ ስትራቴጂ ጋር የተያያዘ መሆኑ ታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውስጥ ምንጮች እንደገለጹት፣ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በቀጠናው ባላቸው የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲ ልምድ፣ በተለይም ቀደም ሲል በጅቡቲ፣ በሴኔጋል እና በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (IGAD) እና በአፍሪካ ህብረት የዩኤን ልዩ መልዕክተኛ ሆነው በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ የሰሩ በመሆናቸው ለዚህ ታላቅ ቀጠናዊ ሚና ተመራጭ አድርጓቸዋል።
ዋና ፀሐፊው አንቶኒዮ ጉተሬዝ ይህንን ውሳኔ ያሳለፉት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ለማርገብ፣ በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር መልሶ ለመገንባት እና የድርጅቱን ቀጠናዊ ተሰሚነት ከፍ ለማድረግ ታስቦ መሆኑ ተጠቁሟል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴም በቅርቡ የስልጣን ዘመናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በተለያዩ አህጉራዊ የግጭት አፈታት እና የሰላም ግንባታ ውይይቶች ላይ በንቃት እየተሳተፉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ይህ ሹመት ዩኤን ለአፍሪካ ቀንድ ቀውስ ዘላቂ መፍትሄ ለመፈለግ በወሰደው ስልታዊ እርምጃ ውስጥ ትልቅ ግምት የተሰጠው ሲሆን፥ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እና የሹመቱን ሙሉ ይዘት እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በሳውላ ከተማ የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን የገባ መምህር እና ተማሪው በቁጥጥር ስር ዋሉ
ሰኔ 11 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሳውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ... read more
የአሥራ አንድ ዓመት ሕፃን ልጅ በማገት 4 ሚሊዮን ብር የጠየቀው በቁጥጥር ሥር ዋለ
ታኅሳስ 08 ቀን 2017 ዓ.ም(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ የአስራ አንድ... read more
በኢትዮጵያ በዘንድሮ አመት 270 ሚሊየን ኮንዶም እንደሚያስፈል ተገለጸ
ኤ.ኤች.ኤፍ ኢትዮጵያ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመቆጣጠር እየሰራ እንዳለ ገልጻል፡፡ ተቋሙ በየትምህርት ቤቶች እና ከትምህርት ቤት... read more
ከቁጥጥር ውጪ የሆነው የኢራን ጦርነት፤ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀውሱን ለማረጋጋት የሚያደርጉት ጥረት ከሽፏል?
ሰኔ 01 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በዩናይትድ ስቴትስ፣ በታሪክ ትልቁ የተባለውና በኦፕሬሽን “ኤፒክ ፉሪ” (Operation Epic Fury) የጀመረው የኢራን ጦርነት፣ ከፕሬዝዳንት... read more
በመዲናዋ የሚተከሉ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃዎች ለስርቆት እንዳይጋለጡ በማይቀልጡ ቁሶች እንዲተኩ እየተደረገ ነው ተባለ
ጥቅምት 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በመዲናይቱ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስታንዳርዱን የጠበቀ የቆሻሻ መጣያ (ደስት ቢን) እንዲተከል ምቹ ሁኔታ የፈጠረ... read more
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ55ኛ መደበኛ ስብሰባው በርካታ ረቂቅ አዋጆችን፣ ፖሊሲዎችንና ደንቦችን አጸደቀ
ግንቦት 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሚኒስትሮች ምክር ቤት ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው 55ኛ መደበኛ ስብሰባው ሀገራዊ ኢኮኖሚን፣ ማኅበራዊ ልማትንና... read more
ታሊባን በመላው አፍጋኒስታን የኢንተርኔት አገልግሎት አቋረጠ፡ ሀገሪቱ ወደ “ጥልቅ አዘቅት” እየተጎተተች ነው ተባለ
መስከረም 20 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአፍጋኒስታን የሚገኘው የታሊባን አስተዳደር በመላ አገሪቱ ያለውን የፋይበር ኦፕቲክ ኢንተርኔት ግንኙነት ማቋረጡ ተዘገበ። ይህ እርምጃ... read more
የማሳጅ ቤቶች ስራ እና የነዋሪው ቅሬታ
👉
https://youtu.be/Ergmq7Iigxw
read more
በተደጋጋሚ ያለምክንያት የሚደወሉ የስልክ መስመሮችን የሚያግድ አሰራር መዘርጋቱ ተገለጸ
ነሐሴ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ያለ ምክንያት ደጋግመው የሚደውሉ የስልክ መስመሮችን የሚያግድ አሰራር መዘርጋቱን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ... read more
ምላሽ ይስጡ