መስከረም 08 ቀን 2019ዓ.ም.(መናኸሪያ ሬዲዮ) የማንቸስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ እሁድ ዕለት በኦልድ ትራፎርድ ማንቸስተር ዩናይትድን 1-0 ባሸነፉበት የደርቢ ጨዋታ ላይ በኤርሊንግ ሀላንድ ብቸኛ ጎል ታግዘው 199ኛውን የማንቹሪያን ደርቢ በድል መወጣታቸው የሚታወስ ነው። ታዲያ በጎሉ ዙሪያ የተነሳውን የVAR ውዝግብ አስመልክተው የሰጡት ምላሽ የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን ትኩረት ስቧል። የዳኞች የበላይ አካል PGMOL በጨዋታው ወቅት የVAR ዳኞች ኤንዞ ፈርናንዴዝ በኦፍሳይድ ስፍራ ሆኖ እንቅስቃሴ በማድረጉ የሀላንድ ግብ መሻር ነበረበት በማለት ለዩናይትድ ይቅርታ መጠየቃቸውን ተከትሎ፣ ማሬስካ ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ጠንካራ አስተያየት ሰጥተዋል። ማሬስካ በ2023 በኦልድ ትራፎርድ ሲቲ 2-1 በተረታበት ጨዋታ ማርከስ ራሽፎርድ በግልጽ ኦፍሳይድ ላይ ሆኖ ኳሱን ሳይነካ በመሮጡ የብሩኖ ፈርናንዴዝ ግብ መጽደቁን በማስታወስ ነው “እኛም ከሶስት ዓመት በፊት ለተቆጠረብን መደበኛ ያልሆነ ግብ እስከዛሬ የPGMOLን ይቅርታ እየጠበቅን ነው” ሲሉ ምላሽ የሰጡት ኤንዞ ማሬስካ በጊዜው አሰልጣኝየነበሩት የአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ምክትል በመሆን ይሰራ እንደነበር ይታወቃል። በተጨማሪም ማሬስካ ቡድናቸው ፊል ፎደን በ23ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከወጣበት በኋላ ለ70 ደቂቃዎች ያህል በ10 ተጫዋች ተከላክሎ እና ተፋልሞ ያመጣውን አስደናቂ ድል ትቶ፣ ትኩረቱን በሙሉ በአንድ የVAR ውሳኔ ላይ ማድረግ “ደካማ አመለካከት” ነው ሲሉ ተናግረዋል። በኳስ ጨዋታ የውሳኔ ስህተቶች አንዳንዴ ወደ አንተ አንዳንዴ ደግሞ በተቃራኒ ቡድን ጸጋ ይዘው ሊመጡ እንደሚችሉና ዳኞች በሰከንዶች ውስጥ ውሳኔ መስጠት ስላለባቸው ስህተት ተፈጥሯዊ መሆኑን አክለው ገልጸዋል። ማንቸስተር ሲቲ አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካን የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ከሾመ በኋላ በዚህ የውድድር ዘመን አስደናቂ ጅማሮን በማሳየት ሁሉንም ጨዋታዎች በድል በመወጣት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን በጎል ክፍያ እየመራ ይገኛል። የማንቸስተር ሲቲው አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ አያይዘው በኮሚኒቲ ሺልድ ጨዋታ ወቅት ባጋጠመው የባት ጉዳት ምክንያት ከሜዳ ርቆ የቆየው የ24 ዓመቱ ቤልጂየማዊ የክንፍ አጥቂ ዠሬሚ ዶኩ (Jeremy Doku) ወደ ሙሉ አካላዊ ብቃት ተመልሶ ለጨዋታ ዝግጁ ለመሆን በጣም መቃረቡን ተናግረዋል። አሰልጣኝ ማሬስካ ስለ ተጫዋቹ አጠቃላይ ሁኔታ ሲናገሩ “ዶኩ ወደ ስብስቡ ለመመለስ በጣም ተቃርቧል፤ በዚህም ደስተኞች ነን፤ ተጫዋቹ ለቡድናችን ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያለው ተጫዋች ነው” ሲሉ ገልጸውታል። ___ ሀሳብ እና‘ሳ‘ፍራለን
Related Posts
«ባሎንዶሩ ለእኔ ነው የሚገባው» ሲል ላሚን ያማል አስተያየቱን ሰጠ
መስከረም 05 ቀን 2019ዓ.ም.(መናኸሪያ ሬዲዮ) የባርሴሎናው ወጣት አጥቂ ላሚን ያማል የ2026 የባሎንዶር ክብር ለእሱ እንደሚገባው በራስ መተማመን የተሞላበት አስተያየት የሰጠ... read more
ቀነኒሳ በቀለ በጉዳት ምክንያት ከለንደን ማራቶን ውጪ መሆኑን አሳወቀ
በአለም አትሌቲክስ ኤሊቴ ፕላቲኒየም ደረጃ ከተሰጣቸው የማራቶን ውድድሮች መካከል አንዱ የለንደን ማራቶን እንደሆነ ይታወቃል። ዘንድሮ ከ55 ሺሕ በላይ ሯጮች ይሳተፉበታል... read more
የሻምፒዮንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ዳሰሳ
በየአመቱ ከሚከናወኑ እና የክለቦች ፉክክር ከሚደምቅበት እንዲሁም በአውሮፓ ውስጥ ሀያሉ ክለብ ለመባል የሚደረግ የክለቦች ትንቅንቅ በተለያዩ የአውሮፓ ግዙፍ ስቴዲየሞች በባውዛ... read more
ከአውሮፓ ስፖርት እና ባህል ፌዴሬሽን የፊታችን ሃምሌ 22 እንደሚካሄድ ተገለፀ
ሐምሌ 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ESCFE ይህ በአውሮፓ የኢትዮጵያ ባህል እና ስፖርት ፌዴሬሽን በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በአንድ... read more
ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ እስከ 2029 የማድሪድ ፕሬዚዳንት ሆነው እንደሚቀጥሉ ታወቀ
ስኬታማ የቢዝነስ ሰው እና የክለብ ፕሬዚዳንት እንደሆኑ የሚነገርላቸው ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ ሮድሪጌዝ ለተጨማሪ 4 አመት የማድሪድ ፕሬዚዳንት ሆነው እንደሚያገለግሉ በፊርማቸው አረጋግጠዋል።
ለፉክክር... read more
ሪካርዶ ካሊያፊዮሪ በዚ የውድድር ዘመን ለ4ኛ ጊዜ ጉዳት እንዳጋጠመው እየተገለፀ ነው
ጥር 05 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ይህ ጣልያናዊ ለጉዳት በጣም ተጋላጭ የሆነ ተጫዋች መሆኑ በተደጋጋሚ ገና ቦሎኛም እያለ የጉዳት ታሪክ በብዛት... read more
የሴቶች ማራቶን ሪከርድ ባለቤቷ ኬንያዊቷ ሩት ጄፒንጌች በጊዜያዊነት መታገዷ ተሰምቷል
ሐምሌ 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ኬንያዊቷ የረጅም ርቀት ሯጭ የሆነችው ሩት ጄፒንጌች በአለም አትሌቲክ ኢንቴግሪቲ ዩኒት ወይም የአለም አትሌቲክስ የውድድር... read more
ማንቸስተር ዩናይትድ በአማዞን ዶኩመንተሪ ሊሰራ የታሰበው ዘጋቢ ፊልም እንዲቋረጥ አድርገዋል ተብሏል
ሐምሌ 01 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ዋናው ምክንያት ሩበን አሞሪም መልበሻ ክፍል ውስጥ ካሜራ እንዳይቀመጥ መፈለጉን ተከትሎ ነው ተብሏል።
Prime amazon የየክለቦች... read more
የሩበን አሞሪም የመጀመሪያው ፈራሚ ዲዬጎ ሊዮን እንደሚሆን ይገመታል
ጥር 05 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የ17 አመቱ ፓራጓዊ ዲዬጎ ሊዮን ክለቡን በመልቀቅ ሴሮ ፖርቴኖን በመልቀቅ ፊርማውን ለማንቸስተር ዩናይትድ ለማስቀመጥ ወደ... read more
የእንግሊዝ ክለቦችን የሚያፋጥጠው የዩሮፓ ሊጉ የፍፃሜ ጨዋታ ዳሰሳ
በክለቦች የውድድር መድረክ ላይ ሁለተኛ እርከን የሚሰጠው የዩሮፓ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በሁለት እጅግ አስከፊ የውድድር ዘመንን ባሳለፉ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች... read more
ምላሽ ይስጡ