መስከረም 08 ቀን 2019ዓ.ም.(መናኸሪያ ሬዲዮ) የማንቸስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ እሁድ ዕለት በኦልድ ትራፎርድ ማንቸስተር ዩናይትድን 1-0 ባሸነፉበት የደርቢ ጨዋታ ላይ በኤርሊንግ ሀላንድ ብቸኛ ጎል ታግዘው 199ኛውን የማንቹሪያን ደርቢ በድል መወጣታቸው የሚታወስ ነው። ታዲያ በጎሉ ዙሪያ የተነሳውን የVAR ውዝግብ አስመልክተው የሰጡት ምላሽ የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን ትኩረት ስቧል። የዳኞች የበላይ አካል PGMOL በጨዋታው ወቅት የVAR ዳኞች ኤንዞ ፈርናንዴዝ በኦፍሳይድ ስፍራ ሆኖ እንቅስቃሴ በማድረጉ የሀላንድ ግብ መሻር ነበረበት በማለት ለዩናይትድ ይቅርታ መጠየቃቸውን ተከትሎ፣ ማሬስካ ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ጠንካራ አስተያየት ሰጥተዋል። ማሬስካ በ2023 በኦልድ ትራፎርድ ሲቲ 2-1 በተረታበት ጨዋታ ማርከስ ራሽፎርድ በግልጽ ኦፍሳይድ ላይ ሆኖ ኳሱን ሳይነካ በመሮጡ የብሩኖ ፈርናንዴዝ ግብ መጽደቁን በማስታወስ ነው “እኛም ከሶስት ዓመት በፊት ለተቆጠረብን መደበኛ ያልሆነ ግብ እስከዛሬ የPGMOLን ይቅርታ እየጠበቅን ነው” ሲሉ ምላሽ የሰጡት ኤንዞ ማሬስካ በጊዜው አሰልጣኝየነበሩት የአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ምክትል በመሆን ይሰራ እንደነበር ይታወቃል። በተጨማሪም ማሬስካ ቡድናቸው ፊል ፎደን በ23ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከወጣበት በኋላ ለ70 ደቂቃዎች ያህል በ10 ተጫዋች ተከላክሎ እና ተፋልሞ ያመጣውን አስደናቂ ድል ትቶ፣ ትኩረቱን በሙሉ በአንድ የVAR ውሳኔ ላይ ማድረግ “ደካማ አመለካከት” ነው ሲሉ ተናግረዋል። በኳስ ጨዋታ የውሳኔ ስህተቶች አንዳንዴ ወደ አንተ አንዳንዴ ደግሞ በተቃራኒ ቡድን ጸጋ ይዘው ሊመጡ እንደሚችሉና ዳኞች በሰከንዶች ውስጥ ውሳኔ መስጠት ስላለባቸው ስህተት ተፈጥሯዊ መሆኑን አክለው ገልጸዋል። ማንቸስተር ሲቲ አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካን የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ከሾመ በኋላ በዚህ የውድድር ዘመን አስደናቂ ጅማሮን በማሳየት ሁሉንም ጨዋታዎች በድል በመወጣት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን በጎል ክፍያ እየመራ ይገኛል። የማንቸስተር ሲቲው አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ አያይዘው በኮሚኒቲ ሺልድ ጨዋታ ወቅት ባጋጠመው የባት ጉዳት ምክንያት ከሜዳ ርቆ የቆየው የ24 ዓመቱ ቤልጂየማዊ የክንፍ አጥቂ ዠሬሚ ዶኩ (Jeremy Doku) ወደ ሙሉ አካላዊ ብቃት ተመልሶ ለጨዋታ ዝግጁ ለመሆን በጣም መቃረቡን ተናግረዋል። አሰልጣኝ ማሬስካ ስለ ተጫዋቹ አጠቃላይ ሁኔታ ሲናገሩ “ዶኩ ወደ ስብስቡ ለመመለስ በጣም ተቃርቧል፤ በዚህም ደስተኞች ነን፤ ተጫዋቹ ለቡድናችን ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያለው ተጫዋች ነው” ሲሉ ገልጸውታል። ___ ሀሳብ እና‘ሳ‘ፍራለን
Related Posts
በክለቦች ትልቁ የውድድር መድረክ በሆነው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ እጅግ በጣም ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ነው ተብሏል
👉ተጠባቂ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታን ይዞ በዛሬው እለት ኤምሬትስ ስቴዲየም ላይ ይመለሳል
አርሰናልን ከ ፓሪስ ሴንት ጄርሜ ጋር የሚያገናኘው ይህ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ... read more
ሞሀመድ ሳላህ ዘንድሮ ከሻምፒዮንስ ሊጉ ይበልጥ ፕሪሚየር ሊጉን ማሳካት እፈልጋለሁ ሲል ሀሳቡን ሰጥቷል
ታኅሳስ 26 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ግብፃዊው ኮኮብ ፍርኦኑ ሞ ሳላህ ዘንድሮ አይቀመሴ አቋም ላይ ነው የሚገኘው። በወርሀ ታኅሳስ ብቻ በ7... read more
አርሰናል ቀጣይ አመት የሚጠቀሙበትን ማልያ ይፋ አድርገዋል
አርሰናል ከአዲዳስ የትጥቅ አምራች ተቋም ጋር ባላቸው ስምምነት መሰረት በየአመቱ የክለቡን ታሪክ ፤ ማንነትን ሊያሳዩ የሚችሉ ዲዛይኖችን በመጠቀም ሁሌም አዲሱ... read more
የሩበን አሞሪም የመጀመሪያው ፈራሚ ዲዬጎ ሊዮን እንደሚሆን ይገመታል
ጥር 05 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የ17 አመቱ ፓራጓዊ ዲዬጎ ሊዮን ክለቡን በመልቀቅ ሴሮ ፖርቴኖን በመልቀቅ ፊርማውን ለማንቸስተር ዩናይትድ ለማስቀመጥ ወደ... read more
ማንቸስተር ሲቲዎች ፍሎሪያን ቪርትዝን ለማስፈረም ከሚደረገው ፉክክር ራሳቸውን አገለሉ
የ22 አመቱ ጀርመናዊ የአጥቂ አማካኝ መስመር ተጫዋች በአሁን ሰአት ከሚፈለጉ ፤ በጣም አስደናቂ እንቅስቃሴን ከሚያደርጉ ተጫዋቾች ተርታ ስሙ ይሰለፋል።
ታዲያ ተጫዋቹን... read more
የአርሰናል እግርኳስ ክለብ የስኬት መንገድ ጠራጊው አንጋፋው አርሰን ቬንገር አዲስ እንዲተገበር ያሰቡት እቅድ ጨዋታ ቀያሪ ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል
ኅዳር 28 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ፈረንሳዊው የቀድሞው አሰልጣኝ አርሰን ቬንገር በአሁን ሰአት በአለም አቀፉ የእግርኳስ አወዳዳሪው አካል ፊፋ chief of... read more
ለአትሌቲክስ ልኡክ ቡድን የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት መርሀግብር ተከናወነ
ሐምሌ 15 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በናይጄሪያ አቡኩታ በተካሄደው የአፍሪካ ከ18 እና 20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ... read more
ሊቨርፑል – ከቶተንሃም
♻️በመናኸሪያ ሬዲዮ 99.1 በቀጥታ ይከታተሉ፡፡
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ወደ ለንደን አቅንቶ ቶተንሃምን ይገጥማል።
ይህንን ጫዋታ ስፖርት... read more
ቲዮ ኸርናንዴዝ ሚላኖች እሱን ባስተናገዱበት መንገድ ደስተኛ አለመሆኑን ለወኪሉ አሳውቋል ተብሏል
ታኅሳስ 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ይህ ፈረንሳዊ የቡድኑ አምበል የኮንትራት ሁኔታው አሳሳቢ እንደሆነ ይታወቃል። በ2026 ውሉ ይጠናቀቃል ስለዚህ ውሉን እንዲያድስ... read more
ካርሎስ አልካራዝ አስደናቂ ድል በማስመዝገብ የግራንድ ስለም ሻምፒዮን መሆኑን አረጋገጠ
በታሪክ ረጅም ሰአት የፈጀው የሮላንድ ጌሮስ የፈረንሳይ ሜዳ ኦፕን ቴኒስ የፍፃሜ ውድድር በስፔናዊው ተስፈኛ የሜዳ ቴኒስ ተወዳዳሪ ካርሎስ አልካራዝ አሸናፊነት... read more
ምላሽ ይስጡ