ነሐሴ 07 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም ዳይሬክተር ዶክተር ብርሃኑ አበራ የሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች የራሳቸው የሆነ ሂደት እንዳላቸው ገልጸው፤ እንደ ማሳያም ከቅድመ-ምልክት ጀምሮ በተደጋጋሚ እና በቁጥር በርከት ብለው የመሬት መፈራረስ የሚያስከትሉትን በማንሳት አብራርተዋል።
ተቋሙ የስነ-መሬት እንቅስቃሴዎችን በቋሚነት በመከታተልና በመመዝገብ ላይ እንደሚገኝም ዳይሬክተሩ አክለዋል። ተቋሙ የክትትልና የጥናት ስራዎቹን ውጤታማ ለማድረግ ከተለያዩ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝና ለአብነትም ከኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ፣ ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር አስማምሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የመመዝገብ አቅም ያላቸውና «ብሮድ ባንድ» በመባል የሚታወቁ ዘመናዊ መሣሪያዎችን በመጠቀም ላይ እንደሚገኙ የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ እነዚህ መሣሪያዎች በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚከሰቱና በሬክተር ስኬል ከ4.5 በላይ የሆኑ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶችን በስፋት የመመዝገብ አቅም ያላቸው ናቸው ብለዋል። አብዛኞቹ መሣሪያዎች ውድ በመሆናቸው በዓለም አቀፍ ድጋፍና በጋራ ትብብር የተገኙ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
ሆኖም ግን የኢትዮጵያ የቆዳ ስፋት ሰፊ በመሆኑና የመሬት መንቀጥቀጥ ስጋት ያለበት ሁኔታ በመኖሩ፣ በዘርፉ የሚሰሩ ባለሙያዎችና ተቋማት ቁጥር አሁንም በቂ አለመሆኑን ዶክተር ብርሃኑ ተናግረዋል።
በርካታ ተቋማትና በቂ የስነ-መሬት ባለሙያዎች የሚያስፈልጉ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ያለው የሰው ኃይል እጥረት ለዘርፉ ትልቅ ፈተና ሆኖ መቀጠሉ ተመላክቷል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በቀሪዎቹ የክረምት ወራት ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደሚኖር ተገለጸ
ነሐሴ 01 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ ባለፉት ሁለት የክረምት ወራት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ መደበኛና ከመደበኛ በላይ የሆነ... read more
ኢትዮጵያ ከዉጭ ስታስገባ የነበረዉን የቃጫ ምርት እስከ 40 በመቶ መቀነሷ ተገለጸ
ኢትዮጵያ በእንሰት ምርት የምትታወቅ እና አምራች ሃገር ብትሆነም ከእንሰት ምርት የሚገኘዉን እና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚዉለዉን ቃጫ በዉጭ ምንዛሬ ከዉጭ ስታስገባ... read more
በሳውላ ከተማ የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን የገባ መምህር እና ተማሪው በቁጥጥር ስር ዋሉ
ሰኔ 11 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሳውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ... read more
ለአይነ ስውራን ቤተሰቦቹ ሲል ብቻውን 4 ኪሎ ሜትር መንገድ የገነባው አባት
መስከረም 09 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) በኔፓል ዳንግ ግዛት በሚገኝ ሳታሌ መንደር ውስጥ የሚኖሩት አቶ ቻንድራቢር ኦሊ፣ ለአይነ ስውር ባለቤታቸውና... read more
በበጀት ዓመቱ ከ1 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን በላይ የቡና ምርት ለመሰብሰብ እየተሰራ ነው ተባለ
ኅዳር 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በዚህ አመት እንደ ሀገር ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን በላይ የቡና ምርት ለመሰብሰብ በትኩረት... read more
የስኳር ወረርሽኝ በኢትዮጵያ፡ 2 ሚሊዮን ተጠቂዎች፣ አሳሳቢ የህክምና አቅርቦትና የግንዛቤ ክፍተት
በአለም አቀፉ የስኳር ፌድሬሽን የተደረገው ጥናት እንደሚያሳየው በኢትዮጵያ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የስኳር ህመም እንዳለባቸውና በዚህም ከአጠቃላይ ህዝቡ 3.3 በመቶ... read more
ባለፉት አስር ቀናት ብቻ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ ለስርቆት መዳረጉ ተገለጸ
ባለፉት አስር ቀናት ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦ.ፒ.ጂ ደብሊው ፋይበር መስመር... read more
ስዊዘርላንድ ከአሜሪካ ጋር የገባችውን የፓትሪዮት ሚሳኤል ስምምነት ልታቋርጥ እንደምትችል አስጠነቀቀች
መጋቢት 24 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በአውሮፓዊቷ ሀገር ስዊዘርላንድ እና በአሜሪካ መካከል ያለው የቢሊዮን ዶላር የጦር መሳሪያ ግዢ ስምምነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ... read more
የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት የመድሃኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች መመሪያ የግሉን ዘርፍ የሚያበረታታ ነው ተባለ
የመመሪያው መፅደቅ በዘርፉ የሚስተዋለውን ክፍተት ለመሸፈን አስፈላጊ እንደሆነ የገለፁት የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ መመሪያው ግንቦት... read more
ምላሽ ይስጡ