ነሐሴ 21 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሲአይኤ ዳይሬክተር ጆን ራትክሊፍ በዚህ ሳምንት ወደ ሞስኮ ምስጢራዊ ጉዞ ያደረጉት ሩሲያ በኔቶ አባል ሀገራት ላይ ጥቃት እንዳታደርስ ለማስጠንቀቅ እንደሆነ ጉዳዩን የሚያውቁ በርካታ አካላት ገልጸዋል። ይህ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው ሩሲያ የኔቶን ጥንካሬ ልትፈታተን ትችላለች የሚሉ የአሜሪካ የደህንነት መረጃዎች ባሉበት ወቅት ነው። እንደ ሲቢኤስ ኒውስ ዘገባ ራትክሊፍ በጉዟቸው ወቅት የኢራን ጉዳይንም ያነሱ ሲሆን፣ በሆርሙዝ ወደብ በኩል የሚደረገው የባህር ትራንስፖርት እንቅስቃሴ ካልተከፈተ ተጨማሪ ማዕቀቦች እንደሚጣሉ አስጠንቅቀዋል። የሲአይኤ ዳይሬክተሩ ምስጢራዊ ጉዞ ይፋ የሆነው ማክሰኞ ዕለት የአሜሪካ አየር ኃይል ጄት በሞስኮ ኤርፖርት ሲያርፍ እና የዲፕሎማቲክ ተርኬድ በከተማዋ ውስጥ ሲንቀሳቀስ ከተከታተለ በኋላ ሲሆን፣ ይህም ራትክሊፍ በኃላፊነታቸው ወደ ሩሲያ ያደረጉት የመጀመሪያው የታወቀ ጉዞ ነው። የአሜሪካ ልዑክ ወደ ሞስኮ እንደሚጓዝ ለዩክሬን አስቀድሞ የተነገረ ሲሆን፣ በጉብኝቱ ወቅት ምንም አይነት ጥቃት እንዳታደርስ መጠየቋን አንድ ከፍተኛ የዩክሬን ባለስልጣን ገልጸዋል። በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሬዲዮ አቅራቢው ግሌን ቤክ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ጉዞውን ያረጋገጡ ቢሆንም፣ ጉዞው ከኢራን ወይም ሩሲያ ኔቶን ለመፈተሽ ከሚኖራት ፍላጎት ጋር እንደማያያዝ እና መደበኛ የሚባል ጉዞ እንደሆነ ገልጸዋል። ትራምፕ አክለውም የሩሲያ እና ዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም ከሚያደርጉት ጥረት አንጻር ከዚህ ጉዞ አንድ ነገር ሊገኝ እንደሚችል ተናግረዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በበኩላቸው ራትክሊፍ ከሩሲያ የደህንነት ባለስልጣናት ጋር መወያየታቸውን ነገር ግን ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር እንዳልተገናኙ ገልጸዋል። የአሜሪካ የደህንነት መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ፕሬዝዳንት ፑቲን በኔቶ ግዛት ውስጥ ቀጥተኛ ወታደራዊ ግጭት ባልሆኑ ትንኮሳዎች፣ እንደ የሳይበር ጥቃቶች፣ የቃላት እና የተደበቁ የጥፋት እርምጃዎች ሊያከናውኑ እንደሚችሉ ተገልጿል። የዚህም ዋና ዓላማ ሙሉ ጦርነት መቀስቀስ ሳይሆን የኔቶን አንድነት እና የትራምፕ አስተዳደር አጋሮቹን ለመጠበቅ ያለውን ቁርጠኝነት መፈተሽ ነው ተብሏል። የባለስልጣናትን ስጋት የጨመሩት የቅርብ ጊዜ የሩሲያ እንቅስቃሴዎች ወደ ሮማኒያ የተደረጉ የድሮን ወረራዎችን፣ ባለፈው ወር ወደ ፖላንድ የሩሲያ ሚሳይልን፣ እንዲሁም በአውሮፖ ውስጥ እየጨመሩ የመጡ የደህንነት ማኮላሸት እና የሳይበር ጥቃቶችን ያካትታሉ። በተጨማሪም ሩሲያ ከኢራን ጋር ያላትን አጋርነት የቀጠለች ሲሆን፣ በአካባቢው ስላሉት የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች ለኢራን የደህንነት መረጃዎችን ከመስጠት ባለፈ ለአመታት በድሮን ማምረት ላይ አብረው ሲሰሩ መቆየታቸው በዘገባው ተጠቅሷል።
__ ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
ምላሽ ይስጡ