ሰኔ 23 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የፈረንሳይ መከላከያ ሚኒስቴር የሀገሪቱን የባህር ኃይል ይበልጥ ለማዘመንና ስልታዊ አቅሟን ለማሳደግ የያዘችው ታላቅ እቅድ አካል የሆነችውንና በኑክሌር ኃይል የምትሰራውን ‘ደ ግራስ’ (De Grasse) የተሰኘች እጅግ ዘመናዊ የባህር ሰርጓጅ መርከብ በይፋ መረከቡ ታውቋል።
በቼርቦርግ የባህር ወደብ የተገነባችውና በውሃ ውስጥ እስከ 5 ሺህ 200 ቶን ክብደት የመሸከም አቅም ያላት ይህቺ ሰርጓጅ መርከብ፤ ፈረንሳይ እድሜጠገብ የሆኑትን የ‘ሩቢስ’ (Rubis) ዝርያ መርከቦቿን ለመተካት ከቀረጸችው የስድስት ሰርጓጅ መርከቦች ፕሮግራም መካከል የመጨረሻዋና እጅግ አስፈሪዋ መሆኗ ተነግሯል።
የባህር ላይ ጥቃቶችን፣ የረጅም ርቀት የስለላ ስራዎችንና ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖችን በልዩ ብቃት የመወጣት አቅም ያላት ይህቺ የ‘ባራኩዳ’ (Barracuda) ዝርያ መርከብ፤ ሙሉ በሙሉ በውሃ ውስጥ ተደብቃ ለ270 ቀናት ያህል ያለ ምንም መቆራረጥ ስራዋን ማከናወን የምትችል ሲሆን 65 የቡድን አባላትንም በውስጧ ትይዛለች። ይበልጥ አስፈሪ የሚያደርጋት ደግሞ በውስጧ የታጠቀቻቸው የባህር ላይ ክሩዝ ሚሳኤሎች፣ የ‘F21’ ከባድ ቶርፔዶዎች እና የ‘Exocet SM39’ የፀረ-መርከብ ሚሳኤሎች መሆናቸውን ወታደራዊ ተንታኞች ገልጸዋል።
የፈረንሳይ የመከላከያ ግዥ ኤጀንሲ (DGA) በበላይነት የመራው ይህ የባራኩዳ ፕሮጀክት፤ በድብቅ የመጓዝ (stealth) እና የረጅም ጊዜ ጽናትን ከኑክሌር አቅም ጋር በማጣመር በአሁኑ ወቅት በአውሮፓ ውስጥ ካሉ እጅግ የላቁና አስፈሪ የኑክሌር ጥቃት ሰርጓጅ መርከብ ንድፎች መካከል ቀዳሚው ተደርጎ ተወስዷል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ማዕድ ማጋራት የሰው ተኮር እሳቤያችን ተግባራዊ ማሳያ ነው 👉ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ማዕድ ማጋራት የሰው ተኮር እሳቤያችን ተግባራዊ ማሳያ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው... read more
በአንድ “እምቢታ” የጣሊያንን ሕግ የቀየረችው የ17 ዓመት ወጣት ድፍረት!
👉ክብርን ለመጠበቅ ደፋሪን ማግባት ግዴታ ነው የተባለችው ፍራንካ ቪዮላ ማን ናት?
ጥቅምት 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የዛሬ ዓመታት በፊት በጣልያን ሲሲሊ ክልል... read more
በዲጂታል ዘርፍ ወጣቶችን ለማብቃትና ለማሰልጠን ዓላማ ያደረገው “አዶናይ ቲክቶክ አካዳሚ” ሊከፈት ነው
ሰኔ 20 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ወጣቶች በፍጥነት እየተለወጠ ያለውን የዲጂታል ዓለም በተሳካ ሁኔታ እንዲቀላቀሉና እንዲያሸንፉ ለማስቻል “አዶናይ ቲክቶክ አካዳሚ” ሥራ... read more
ትራምፕ በውጭ አገር በተሠሩ ፊልሞች ላይ የ100% ቀረጥ ሊጥሉ ነው
መስከረም 20 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአሜሪካ ውጪ በሚመረቱ ሁሉም ፊልሞች ላይ የ100 በመቶ ቀረጥ (ታሪፍ) ለመጣል... read more
የክረምት ወቅት መግባትን ተከትሎ በቋሚነት ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎችን የመለየት እና ምላሽ የመስጠት ስራ እየተሰራ ነው ተባለ
ሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በክረምት ወቅት የተፈጥሮ አደጋዎች በስፋት ማጋጠማቸው የሚታወስ ነው፡፡
በተመሳሳይ በዘንድሮ አመት ለሚያጋጥም የተፈጥሮ... read more
“ሶላር ኢምፐልስ 2” የተባለች አውሮፕላን በፀሐይ ኃይል ብቻ ዓለምን በመዞር ክብረ ወሰን ሰበረች
👉በዜሮ ነዳጅ፣ በዜሮ ልቀት 40,000 ኪሎሜትሮችን በአንድ ጊዜ መብረር ያስችላታል ነው የተባለው
ሐምሌ 08 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በአቪዬሽን ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው... read more
በክልሉ የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የምክክር ሂደት እንዳይካሄድ ለማደናቀፍ የሚሰሩ አካላት እኩይ ተግባራቸውን ቢቀጥሉም፤ ህዝቡ ጦርነትን እምቢ እንዲልና ከሰላም ፈላጊው ጎን እንዲቆም ጥሪ ቀረበ
ሐምሌ 29 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢትዮጵያ ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል የሚካሄደውን የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የምክክር ሂደት እንዳያከናውን እንቅፋት ለመሆን የሚሰሩ... read more
ቤተሰብን ለመደገፍ በሚሰራው ስራ የመዋቅርና የፖሊሲ ማዕቀፍ ችግር መኖሩ ተገለጸ
ቤተሰብን በመደገፍ ስራ ውስጥ የመዋቅርና የፖሊሲ ማዕቀፍ ችግር መኖሩን ለጣቢያችን የገለጸው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው።
ኢትዮጵያ አለም አቀፍ የቤተሰብ ህጎችን... read more
የብሔር ተኮር የፌዴራሊዝም ስርዓቱ ምን ያህል የብሔር ብሔረሰቦችን መብት አስጠብቋል?
በሀገራችን ኢትዮጵያ የዜጎች አኗኗር ከቀን ወደ ቀን መልክ እና ሁኔታ እየቀያየረና እየተባባሰ ስለምጣቱ በርካታ ማሳያዎች አሉ። ለዚህም በምክንያትነት የሚነሳው የብሔር... read more
የውጊያ ጄት በትምህርት ቤት ውስጥ ተከስክሶ ቢያንስ 19 ተማሪዎች ሲሞቱ ከ50 በላይ የሚሆኑት መቁሰላቸው ተገለጸ
👉የብሔራዊ ሃዘን ቀን ታውጇልም ተብሏል
ሐምሌ 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በባንግላዲሽ ዋና ከተማ ዳካ በሚገኝ አንድ የኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ የባንግላዲሽ አየር... read more
ምላሽ ይስጡ