ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ በፋይናንስ ዘርፍ ላይ ያሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ወደ አገር ውስጥ ገብተው ሥራ እንዲጀምሩ አዋጅ መዘጋጀቱን ተከትሎ፣ የአገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት እንዳይዳከሙ መጠናከር እንደሚገባቸው በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማት ለጣቢያችን ገልጸዋል።
በአገር ውስጥ ያለው የፋይናንስ አሠራር እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ አገር በቀል የሆኑ የፋይናንስ ተቋማት ማደግ በሚገባቸው ልክ እንዳያድጉ ማድረጉን የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ የኢንተርፕራይዝ ማኔጅመንት ዳይሬክተር አቶ ፍሥሐ ተስፋዬ ገልጸዋል። በአንጻሩ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ የተሰማሩ ተቋማት በጋራና በጥምረት ሊሠሩባቸው የሚችሉ ጉዳዮችን በመለየት ማጠናከር እንደሚገባቸው ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ በርካታው የማኅበረሰብ ክፍል የሚገኘው በአገሪቱ ገጠራማ አካባቢዎች ላይ እንደመሆኑ፣ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ የኅብረት ሥራ ተቋማት አቅማቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የኢንፊኒቲ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ተቋም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ እስክንድር መኩሪያ ይገልጻሉ። በተለይም ደግሞ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ የሚስተዋለው የትብብር ማነስ፣ የጥሬ ገንዘብ እጥረትና ተደራሽነት፣ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማት ጥቂት መሆን ሊሻሻሉ የሚገቡ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።
የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ዶክተር ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ወደ አገር ውስጥ ገብተው ሥራ መጀመራቸው ለትልልቅ የኢንቨስትመንት ሥራዎች እና ለውጭ ምንዛሬ አቅርቦት በጎ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ተናግረዋል። ከሰሞኑ በኢንቨስትመንት ባንክ ሥራ ላይ የተሰማራው የናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል ግሩፕ በካፒታል ገበያ ላይ ሕጋዊ ፈቃድ ያገኘ ሲሆን፣ በቀጣይም በኢትዮጵያ በባንክ አገልግሎት ዘርፍም ሆነ በኢንሹራንስ ዘርፍ የተሰማሩ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ፈቃድ አግኝተው ሥራ ሲጀምሩ ለኢኮኖሚው ጠቃሚ እንደሚሆኑና በአገር በቀል ባንኮች ላይ ጫና እንደማያሳድሩ አመላክተዋል።
የውጭ አገር ባንኮች በአገር ውስጥ ገብተው እንዲሠሩ የሚፈቅደው አዋጅ መጽደቁ የሚታወስ ሲሆን፣ የኢንሹራንስ ድርጅቶች እንዲሠሩ የሚፈቅደው ረቂቅ አዋጅም በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ዳሰሳየአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እድልና ስጋቱ
https://youtu.be/nV0MajqiGnc
read more
የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ህልፈት የተሰማትን ሀዘን ገለፀች
የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን እና በዚህም ቤተክርስቲያኗ የተሰማትን ሀዘን ገልጻለች።
ቤተክርስቲያኗ በማህበራዊ... read more
ከፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጋር የተፈጠረውን አለመግባባት ተከትሎ አሜሪካ ለዩክሬን የምትሰጠውን ወታደራዊ እርዳታ ለአፍታ ማቆሟን አስታወቀች
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ሳምንት ከዩክሬን አቻቸው ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በቤተ-መንግስት ያልተግባቡበትን ንግግር ካደረጉ በኋላ ለዩክሬን የሚሰጠውን ወታደራዊ እርዳታ... read more
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ያለማንም የውጭ ገንዘብ ድጋፍ እና ብድር በኢትዮጵያዉያን የተሰራ መሆኑ ተገለጸ
ሐምሌ 15 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ታላቁ የአኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በማህበረሰቡ ተሳትፎ እንጂ የየትኛውም አለም ሀገራት ገንዘብ ያልተካተተበት መሆኑን የህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ... read more
የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን አካታችነት ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየሰራ መሆኑን እየገለጸ ቢሆንም “አስተርጓሚን ጨምሮ በብሬል የተዘጋጀ መረጃ የለም፤መሰብሰቢያ አዳራሾቹና መጸዳጃ ቤቶቹ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ አይደሉም” የሚል ቅሬታ ቀርቦበታል
♻️“በሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ውይይት ወቅት አስተርጓሚን ጨምሮ በብሬል የተዘጋጀ መረጃ የለም፤ መሰብሰቢያ አዳራሾቹና መጸዳጃ ቤቶቹ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ አይደሉም”- አካል... read more
በትግራይ ክልል የሜርኩሪ መርዛማ ኬሚካል በከፍተኛ ሁኔታ አደጋ እያደረሰ መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ በማዕድን ዘርፍ ላይ በተደረገ ጥናት በአከባቢው የሜርኩሪ መርዛማ ኬሚካል አጠቃቀም ከፍተኛ አደጋ እያደረሰ መሆኑን ለመናኸሪያ ሬዲዮ የገለጹት በትግራይ ክልል... read more
ዲጂታልን ታሳቢ ያላደረጉ ህጎች መሻሻል እንደሚኖርባቸው ተገለጸ
ሐምሌ 17 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ከዚህ ቀደም የወጡ አንዳንድ ህጎች ዲጂታልን ታሳቢ አድርገው የተዘጋጁ ባለመሆናቸው በዘርፉ ከፍተኛ ክፍተት መፈጠሩን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ... read more
ወደ ዲጂታል የተቀየረው የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ያስነሳው ቅሬታ
👉
https://youtu.be/6hCukbezdjE
read more
“ሚሳኤሎቻችን ባይኖሩ ኖሮ እንደ ጋዛ እንሆን ነበር” — የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን
ሰኔ 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ሀገራቸው የያዘችው የባሊስቲክ ሚሳኤል ፕሮግራም በፍፁም ለድርድር የማይቀርብ መሆኑን በፅኑ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ... read more
በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የሰጠው ውክልና የለም ተባለ
ኅዳር 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) “ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፤ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል” በሚል በተለያዩ የማህበራዊ... read more
ምላሽ ይስጡ