ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸው የባህር ኃይል ክፍሏን በታክቲካል የኒውክሌር መሳሪዎች ለማስታጠቅ እና ይበልጥ ግዙፍ የሆኑ ዘመናዊ የጦር መርከቦችን ለመገንባት በከፍተኛ ፍጥነት እየሰራች መሆኑን በይፋ ተናገሩ። መሪው ይህንን ያሉት ሀገሪቱ ባለፈው ዓመት የገነባቻቸው እና በሬክተር ስኬል 5 ሺህ ቶን የሚመዝኑት ሁለት ግዙፍ አጥፊ የጦር መርከቦች መካከል አንደኛዋ የሆነችው “ቾይ ሂዮን” (Choe Hyon) በይፋ ስራ በምትጀምርበት የሹመት ስነ-ስርዓት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው።
ኪም ጆንግ ኡን በናምፖ የወደብ ከተማ በተካሄደው በዚህ ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ የባህር ኃይሉን በኒውክሌር የመሳሪያ ስርዓቶች የማደራጀቱ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ያለምንም መስተጓጎል በተያዘለት መስመር እየተጓዘ ይገኛል። ይህ እርምጃ የሰሜን ኮሪያን የኒውክሌር ኃይል ለማንኛውም ዓይነት ሁለገብ እና ፈጣን ወታደራዊ እርምጃ ዝግጁ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን መሪው በኩራት ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሀገሪቱ በየዓመቱ ሁለት ግዙፍ የጦር መርከቦችን የምትገነባ ሲሆን፥ ወደፊትም እስከ 10 ሺህ ቶን የሚመዝኑ እጅግ ግዙፍ ስልታዊ የጦር መርከቦችን በቅደም ተከተል ወደ ስራ እንደምታስገባ ይፋ አድርገዋል።
ሰሜን ኮሪያ ቀደም ሲል ባወጣችው መግለጫ አዲሷ “ቾይ ሂዮን” የተባለችው የጦር መርከብ የሀገሪቱን እጅግ “ኃያላን መሳሪዎች” የታጠቀች መሆኑን ያረጋገጠች ሲሆን፥ መርከቧ የኒውክሌር ዶንጓዴዎችን እና የክሩዝ ሚሳኤሎችን ጭኖ የመተኮስ ከፍተኛ አቅም እንዳላት ተገልጿል። ይህ በሰሜን ኮሪያ በኩል የታየው አዲስ የባህር ኃይል መዋቅር ሽግግር በአከባቢው በአሜሪካ እና በደቡብ ኮሪያ የሚደረጉ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የታለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የኪም ጆንግ ኡን አዲስ ወታደራዊ አዋጅ በኮሪያ ባህረ-ሰላጤ ላይ ያለውን የደህንነት እና የፖለቲካ ውጥረት ይበልጥ ወደ ከፋ ደረጃ ያሸጋግረዋል ተብሎ የተፈራ ሲሆን፥ በጉዳዩ ዙሪያ የሚወጡ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እንደደረሱን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ሞርተን ዩልማንድ አትሌቲኮን ለመቀላቀል መስማማቱ ተዘግቧል።
ሐምሌ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአትሌቲኮ ማድሪድ ክለብ የፖርቹጋሉን ስፖርቲንግ ሊዝበን አምበል እና የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን አማካኝ ሞርተን ዩልማንድን ለማስፈረም የተቃረበ... read more
አፍሪካ ዉስጥ በጎች እና ፍየሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሰውን አስከፊ ቫይረስ (ፔስቴ ዴስ ፔቲትስ ሩሚናንት)(PPR) ለመዋጋት የፓን አፍሪካን ፕሮግራም ተጀመረ
አዲስ አበባ በጥር ወር መጨረሻና በየካቲት ወር መጀመሪያ ላይ የአፍሪካ ህብረት ታላላቅ ግቦች እና የፓን አፍሪካ አጀንዳዎች ጋር የተጣጣሙ ወሳኝ... read more
በማርበርግ በሽታ ከተያዙ 11 ሰዎች ውስጥ 6ቱ በበሽታው ህይወታቸው ማለፉ ተገለጸ
ሕዳር 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ከህዳር 5/ 2018 ዓ.ም ጀምሮ የማርበርግ ህክምና ምርመራ ሲደረግ የቆየ ሲሆን በበሽታው ከተጠቁ 11 ሰዎች... read more
የጎዳና ተዳዳሪዎችን ሙሉ መረጃ የማስመዝገብ ግዴታ ለሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደተሰጠው ተገለጸ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 18ኛ መደበኛ ስብሰባውን በትላንትናው እለት ባካሄደበት ወቅት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የጎዳና... read more
የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሆኑ መሳሪያ አንግበው ግጭት ውስጥ ያሉ ቡድኖች በአገራዊ ምክክሩ የአጀንዳ ማሰባሰብ እንዲሳተፉ ኮሚሽኑ ተደጋጋሚ ጥሪ ማቅረቡን እንደሚቀጥል ገልጿል
ታኅሳስ 08 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኦሮሚያ ክልል ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ ምዕራፍ በአዳማ ከተማ መካሄዱን ቀጥሏል፡፡
ከክልሉ 356 ወረዳዎች የተመረጡ ከ7... read more
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲጠናከር ማስቻሉ ተገለጸ
ሐምሌ 28 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ የአገርን የደን ሽፋን መጠን በማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥን ተከትሎ ሊከሰት የሚችለውን... read more
ባለፉት አስር ቀናት ብቻ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ ለስርቆት መዳረጉ ተገለጸ
ባለፉት አስር ቀናት ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦ.ፒ.ጂ ደብሊው ፋይበር መስመር... read more
ማይክሮፕላስቲኮችን ከውሃ አካላት የሚሰበስብ ሮቦቲክ ዓሳ በዩኒቨርሲቲ ተማሪ ተሰራ
ሐምሌ 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በዓለማችን ላይ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ በሚደረገው ጥረት አዲስ ተስፋ የሚሰጥ ፈጠራ ይፋ ሆነ። "ጊልበርት" የተባለ ማይክሮፕላስቲኮችን... read more
በሕፃፅ መጠለያ ለሚገኙ ተፈናቃዮች የተላከው የዕርዳታ እህልና ገንዘብ የት ገባ?
ታህሳስ 14 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሕፃፅና አካባቢው በመጠለያ የሚገኙ ማህበረሰቦች በከፍተኛ የረሃብና የችግር አዙሪት ውስጥ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ላለፉት አራት... read more
በአማራ እና ትግራይ ክልል ያሉ የተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያዎች ቀጣዩን የክረምት ወቅት ዝናብ እና ጎርፍ መቋቋም እንደማይችሉ ተገለጸ
በተለያዩ ጊዜያት በሀገሪቱ የተከሰቱትን ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ተከትሎ በርካታ ዜጎች በመጠለያ ጣቢያዎች እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ ቀጣዩን የክረምት ወቅት ተከትሎ... read more
ምላሽ ይስጡ