መስከረም 08 ቀን 2019ዓ.ም.(መናኸሪያ ሬዲዮ) ከሃምሳ ሺህ በላይ ተሳታፊዎች ይሳተፉበታል ተብሎ የሚጠበቀው ሁለተኛው ታላቁ የኢሬቻ ሩጫ መስከረም 21 ቀን 2019 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ እንደሚካሄድ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታውቋል። የኦሮሚያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ቢያ ለውድድሩ አሸናፊዎች ከፍተኛ የሆነ ሽልማት መዘጋጀቱን በመግለጽ፣ በዚህም በሁለቱም ጾታዎች ለአንደኛ ለወጡት አንድ አንድ ሚሊዮን ብር፣ ለሁለተኛ ሰባት መቶ ሺህ፣ ለሦስተኛ አምስት መቶ ሺህ እያለ እስከ ስድስተኛ ለሚወጡት ሽልማት እንደተዘጋጀላቸው ገልጸዋል። ውድድሩ አስር ኪሎሜትሮችን የሚሸፍን ሲሆን፣ የዲባባ ቤተሰቦች የዚህ ዓመት የውድድሩ ብራንድ አምባሳደሮች መሆናቸውን አስረድተዋል። በዚህ ዓመትም ኢሬቻን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ብቸኛው ውድድር መሆኑን በመግለጽ፣ የተወዳዳሪዎች የምዝገባ ቦታዎች በአዲስ አበባ፣ በአዳማ እና በቢሾፍቱ ከተሞች እንደሚካሄዱ ተናግረዋል። የኦሮሞ አባገዳዎች ኅብረት ዋና ጸሐፊ አባገዳ ጌቱ ተሊላ ሁሉም በአንድነት ሩጫው ላይ እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ አቶ አለማየሁ አሰፋ በበኩላቸው ሩጫውን ጨምሮ ለኢሬቻ ክብረ በዓል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የመጀመሪያው ታላቁ የኢሬቻ ሩጫ በ2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወሳል። ___ ሀሳብ እና‘ሳ‘ፍራለን
Related Posts
በእንግሊዝ የሚገኙ በቀቀኖች ጎብኚዎችን እየተሳደቡና እየተሳለቁ በማስቸገራቸው ተቀጡ
ታህሳስ 15 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በእንግሊዝ በሚገኝ አንድ የእንስሳት ማቆያ ውስጥ የሚገኙ አምስት የአፍሪካ ግራጫ በቀቀኖች ወደ ስፍራው የሚመጡ ጎብኚዎችን... read more
በኢንዶኔዥያ እስላማዊ ፍርድ ቤት ሁለት ወጣቶች መተቃቀፍና መሳሳም በሚል ተከሰው 80 ጊዜ በጅራፍ ተገረፉ
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በኢንዶኔዥያ የኤሴህ ግዛት የሚገኝ አንድ እስላማዊ ፍርድ ቤት፣ ሁለት ወንዶች ልጆችን በህዝብ ፊት እንዲገረፉ ፈረደባቸው። እነዚህ... read more
የከተማ አውቶቡስ ትራንስፖርት አገልግሎት እስከ ምሽት 4 ሰዓት መራዘሙ ተገለጸ
ኅዳር 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በእጅጉ እየፈተኑ ከሚገኙ ጉዳዮች መካከል አንዱ የትራንስፖርት እጥረት መሆኑ ይታወቃል፡፡ መንግስት የትራንስፖርት... read more
ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ በሽብር ወንጀል ተጠርጣሪዎች ላይ የ14 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ ተፈቀደ
ፍርድ ቤቱ ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የ14 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል፡፡
ፖሊስ ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት... read more
ማንቸስተር ዩናይትድ በአክዜል ቱዋንዜቤ ጉዳይ ክስ ቀርቦባቸዋል
ሕዳር 04 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ማንችስተር ዩናይትድ የቀድሞ ተጫዋቹን አክሰል ቱዋንዜቤን ጉዳት በሚገባ እንዲከታተል ሁኔታዎችን ባለማመቻቸት ወይም ባሳዩት ግዴለቅነት የተሞላበት ድርጊት... read more
ስፔስኤክስ የመጀመሪያውን የሩብ ዓመት የገቢ ሪፖርት ማቅረቡን ተከትሎ የአክሲዮን ዋጋው በ13 በመቶ ቅናሽ አሳየ
ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢሎን መስክ ኩባንያ የሆነው ስፔስኤክስ (SpaceX) እንደ ይፋዊ ኩባንያ የመጀመሪያውን የሩብ ዓመት የገቢ... read more
ፓርቲው ከተሰረዘ በኋላ የሚያደረጋቸው የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ኢ-ህገ መንግስታዊ እንደሚሆን ተገለጸ
አንድ ፓርቲ ከምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅናውን ካጣ በኋላ የሚያደርገው ማንኛውም እንቅስቃሴ ኢ-ህገ መንግስታዊ ይሆናል ሲሉ የህግና የፌዴራሊዚም ባለሙያዎች ለመናኸሪያ ሬዲዮ... read more
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጠቃላይ ሐብት 2.073 ትሪሊዮን ብር ደረሰ
👉ባለፉት ስምንት ወራት ከ7.72 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች መከናወኑም ተመላክቷል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጠቃላይ ሐብት... read more
በጅቡቲ ድንበር ህይወታቸው የሚያልፍ አሽከርካሪዎችን አስክሬን ለማንሳት የሚጠየቀው ገንዘብ ከፍተኛ በመሆኑ ችግሩ አሳሳቢ ሆኗል ተባለ
ሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በኢትዮጵያ የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች እየደረሰባቸው ካለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ባለፈ ጠረፍ አካባቢ ያለው ከፍተኛ የሙቀት... read more
ምላሽ ይስጡ