ነሐሴ 27 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አምስቱም የጳጉሜን ቀናት የእምርታ፣ የማንሰራራት፣ የፅናት፣ የህብርና የነገ ቀን በሚል ልዩ ስያሜ እንደሚከበሩ አስታውቋል። ጋዜጣዊ መግለጫውን የሰጡት የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ ሁሉም ቀናት በወጣላቸው ስያሜ መሠረት ይከበራሉ ብለዋል። አምስቱም የጳጉሜን ቀናት የየራሳቸው ስያሜ ይውጣላቸው እንጂ ማንሰራራትን ከግምት ውስጥ በማስገባት እየተጠናቀቀ ባለው ዓመት የተመዘገቡ ትልልቅ ስኬቶችን መሠረት በማድረግ እንደሚከበሩ ገልጸዋል። በእነዚህ የጳጉሜን ቀናት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና የነበሩ ተግዳሮቶችን በመገመገም ለቀጣይ ጊዜያት ለዝግጅትነት መጠቀም እንደሚገባም አፅንኦት ሰጥተዋል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
ምላሽ ይስጡ