ሐምሌ 30 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ኢኳዶር፣ ባባሆዮ በተባለች ከተማ የሚገኘው ማርቲን ኢካዛ ሆስፒታል ሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ.ም አንድ ያልተለመደና አሳዛኝ ክስተት አስተናግዷል። እድሜያቸው 76 የሆኑት አያት ቤላ ሞንቶያ በጽኑ ታመው ወደ ሆስፒታሉ ከገቡ በኋላ፣ በወቅቱ በነበሩት ሀኪሞች “ህይወታቸው አልፏል” የሚል ኦፊሴላዊ የሞት ምስክር ወረቀት ተሰጣቸው።
የሞታቸውን ዜና የሰሙት ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው የቀብር ስነ-ስርዓታቸውን ለመፈጸም አስከሬኑን በሬሳ ሳጥን ውስጥ አድርገው ወደ ቀብር ማዘጋጃ ቤት ወሰዱት። ለሰዓታት ያህል የሀዘን ስነ-ስርዓት ሲካሄድ ቆይቶ፣ ከቀብሩ በፊት የሬሳ ሳጥኑን ከፍተው ልብሳቸውን ለመቀየር ሲዘጋጁ ግን ያልተጠበቀ ድንጋጤ ተከሰተ።
የአያት ቤላ ሞንቶያ ልጅ የሆነው ጊልበርት ባልቤራን እንደተናገረው፣ ከሰዓታት ሀዘን በኋላ ከሳጥኑ ውስጥ ደካማ ማንኳኳትና የመተንፈስ ድምፅ መሰማት ጀመረ። ቤተሰቦቻቸው ሳጥኑን በፍጥነት ሲከፍቱ፣ አያት በህይወት ሆነው ግራ እጃቸውን በማንቀሳቀስና አፋቸውን በመክፈት አየር ለማግኘት ሲታገሉ ተመለከቱ።
ይህ ክስተት በወቅቱ በሆስፒታሉ ባለሙያዎች ዘንድ ከፍተኛ መደናገጥን የፈጠረ ሲሆን፣ አያት ወዲያውኑ ወደ ጽኑ ህክምና ክፍል ተመልሰው ኦክስጅን እንዲያገኙ ተደረገ። የህክምና ባለሙያዎች እንደሚሉት አያት የካታሌፕሲ (Catalepsy) ተብሎ በሚጠራ የነርቭ መታወክ ሁኔታ ውስጥ ወድቀው የነበረ ሲሆን፣ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ያለ ሰው የልብ ምቱና የመተንፈስ ፍጥነቱ እጅግ አነስተኛ ከመሆኑ የተነሳ እንደ ሞተ ሰው ተቆጥሮ በስህተት ሊደመደም ይችላል።
ክስተቱን ተከተሎ የኢኳዶር ጤና ሚኒስቴር አያት በስህተት ሞተዋል ተብለው የሞት ምስክር ወረቀት እንዴት ሊሰጣቸው እንደቻለ ለማጣራት ብሔራዊ ኮሚቴ አቋቁሞ ምርመራ ጀምሮ ነበር።
ሆኖም ግን፣ አያት ቤላ ሞንቶያ በጽኑ ህክምና ክፍል ውስጥ ለአንድ ሳምንት ያህል ከቆዩ በኋላ ሰኔ 16 ቀን 2015 ዓ.ም በተከሰተ የstroke ችግር ምክንያት ህይወታቸው ማለፉ በይፋ ተረጋግጧል።
የመጀመሪያው አጋጣሚ ግን በዓለም አቀፍ ደረጃ በህክምና ታሪክ ውስጥ እጅግ አስገራሚና በማህበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ መነጋገሪያ ከሆኑ ክስተቶች አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በትግራይ ክልል በተካሄደው የ8ተኛ ክልል አቀፍ ፈተና ይሳተፋሉ ተብሎ ከተጠበቀው 50 በመቶ የሚሆኑት አለመሳተፋቸው ተገለጸ
ታኅሳስ 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል በጦርነት ምክንያት ተማሪዎች በመደበኛ የትምህርት ሰዓት እየተማሩ አለመሆኑ እና የፈተና ሰዓትም ጠብቀዉ እየተፈተኑ... read more
የአርበኞች ቀንን በልዩ መልኩ ለማክበር በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ
ዘንድሮ ለ84ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአርበኞች ቀንን ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ፋሽስተ ኢጣሊያን በስተመጨረሻ በተሸነፈበት ቦታ ለማክበር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የኢሉ አባበር... read more
‘‘በደብረጽዮን የሚመራው ህወሓት ከኤርትራ መንግስት ጋር እየሰራ ነው’’ – ጊዜያዊ አስተዳደሩ
የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራር ከሆኑት ከአቶ #ጣዕመ #አረዶም ጋር የተደረገ ቆይታ
https://youtu.be/F1ilWPpFztU
read more
ህፃን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በ13 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
አሳምነው ስዩም ታምራት የተባለ የ40 ዓመት እድሜ ያለው ግለሰብ 1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 627/1/፤/4/(ሀ) ላይ የተደነገገውን ህግ በመተላለፍ... read more
በታክስ ስወራ፣ የተጨማሪ ታክስ አለመክፈል፣ በኮንቶሮባንድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተከሰሱ
ታኅሳስ 18 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በታክስ ስወራ፣ የተጨማሪ ታክስ አለመክፈል፣ በኮንቶሮባንድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀል... read more
በጀርመን እስረኛ ከእስር ለማምለጥ ቢሞክር ወንጀል አይደለም ተባለ
👉ነጻነትን የማግኘት ሙከራ ሰብዓዊ መብት ነው ተብሏል
ሐምሌ 29 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የጀርመን የፍትህ ስርዓት በአንድ አስገራሚና ልዩ ህግ ይታወቃል የተባለ ሲሆን... read more
ለነዳጅ ኩባንያዎች እና ማደያዎች ወደ ህጋዊ ስርዓት እንዲገቡ ማሳሰቢያ ተሰጣቸዉ
በህገ-ወጥነት ተግባር ላይ የተሰማሩ የነዳጅ ኩባንያዎች እና ማደያዎች ወደ ህጋዊነት እንዲገቡ ማሳሰቢያ መሰጠቱን የገለጹት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶክተር ካሳሁን... read more
አስተግባሪ ያጣው የትንባሆ ቁጥጥር
👉
https://youtu.be/e-KBshnYaRk
read more
በፀሐይ ኃይል የሚሰራው ግዙፉ የመኪና ማጓጓዣ መርከብ የመጀመሪያ ጉዞውን አጠናቀቀ
ሰኔ 28 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የዓለማችን ትልቁ በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የመኪና ማጓጓዣ መርከብ "ዩዋን ሃይ ኮው" (Yuan Hai Kou) የመጀመሪያ ጉዞውን... read more
“በጸጥታና ደህንነት ተቋማት ያከናወነው የሪፎርም ስራ ኢትዮጽያን የሚመጥንና ዘመን ተሻጋሪ ተቋማትን ለመገንባት ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው። የኢትዮጵያ አየር ኃይል ደግሞ በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ነው። አየር ኃይሉ 89ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ ባለበት በዚህ ወቅት ”ጸሐይ 2 ” የተሰኘችና በአየር ኃይሉ የተሰራች አውሮፕላን ለበረራ ብቁ አድርጓል። አውሮፕላኗ ግዳጅን በብቃት መፈጸም የሚያስችል ቴክኖሎጂ የታጠቀች ናት። ይህም አየር ኃይሉ በ2030 በአፍሪካ ስመጥር አየር ኃይል ለመሆን የያዘውን ራዕይ እውን ለማድረግ በትክክለኛ ጎዳና ላይ መሆኑን የሚያመላክት ነው።” 👉ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ
__
ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን
መናኸሪያ ሬዲዮ 99.1
ሃሳብ፣አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት የሚከተሉትን የስቱዲዮ ስልኮቻችን ይጠቀሙ
👉011-639-28-52👉011-639-37-63
የቀጥታ ስርጭት 👉 📻 (https://worldradiomap.com/et/play/menaharia) radio 99.1 (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
✅ Telegram (https://t.me/menaharia_fm)
ትክክለኛውን... read more
ምላሽ ይስጡ