ሐምሌ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአትሌቲኮ ማድሪድ ክለብ የፖርቹጋሉን ስፖርቲንግ ሊዝበን አምበል እና የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን አማካኝ ሞርተን ዩልማንድን ለማስፈረም የተቃረበ ሲሆን፣ በግል ጥቅማጥቅሞች ዙሪያ ከተጫዋቹ ጋር ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ማትዮ ሞሬቶ እንደዘገበው፤ አትሌቲኮ ማድሪድ ከሊዝበን ጋር የነበረው የ35 ሚሊዮን ዩሮ የመጀመሪያ ጥያቄ ውድቅ ከተደረገበት በኋላ፣ አጠቃላይ የዝውውር ሂሳቡን ወደ 40 ሚሊዮን ዩሮ (35 ሚሊዮን ቋሚ እና 5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ማበረታቻዎች) በማሳደግ ተጫዋቹን ለማስፈረም ተቃርቧል።
የ26 ዓመቱ አማካኝ እስከ 2031 ዓ.ም የሚያቆየውን የ5 ዓመት ኮንትራት ለመፈረም የተስማማ ሲሆን፣ በአዲሱ ክለቡ የቅድመ-ውድድር ዝግጅት ለመጀመር ወደ ማድሪድ ያመራል ተብሎ ይጠበቃል። አትሌቲኮ ማድሪድ ፊቱን ወደ ዩልማንድ ያዞረው፣ ከዎልቭሱ ጆአኦ ጎሜስ ወኪል ጆርጅ ሜንዴስ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ተከትሎ የዝውውር እቅዱን በመቀየሩ ነው።
ሞርተን ዩልማንድ ባለፈው የ2025/2026 የውድድር ዘመን በፖርቹጋል ፕሪሜራ ሊጋ እና በተለያዩ ውድድሮች ለስፖርቲንግ ሊዝበን በአማካኝ መስመር ላይ ቁልፍ ሚና የነበረው ሲሆን፣ 1 ግብ አስቆጥሮ 1 ለግብ የሚሆን ኳስ ማመቻቸት ችሏል።
አትሌቲኮ ማድሪድ ይህንን ተጫዋች አጥብቆ የፈለገበት ዋነኛው ምክንያት በአሰልጣኝ ዲዬጎ ሲሚዮኒ የጨዋታ ስልት ውስጥ ጠንካራ፣ ኳስ አስጣይ እና መከላከል ላይ ያተኮረ ንቁ የተከላካይ አማካኝ (Defensive Midfielder) እንዲሁም በተከላካይ እና በአጥቂ መስመር መካከል ድልድይ የሚሆን ተጫዋች ስለሚያስፈልገው ነው።
ዩልማንድ በስፖርቲንግ ሊዝበን መሪነቱን እና የአማካኝ ክፍሉን በአግባቡ የመቆጣጠር ብቃቱን ያሳየ በመሆኑ፣ ሲሚዮኒ ለሚገነቡት አዲስ የአማካኝ መስመር ጥንካሬ ዋነኛ ምርጫቸው አድርገውታል፤ ተጫዋቹም በሮጂብላንኮዎቹ ቤት ለ5 ዓመታት የሚያቆየውን ኮንትራት ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ባለፉት አመታት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበር ከመቀዛቀዝ ባለፈ በእዳ ምክንያት የሚሰራበት ቢሮ ተዘግቶ እንደነበር አስታወቀ
ጥቅምት 10 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበር ከቀናት በፊት 4ተኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አከናውኗል።
መናኸሪያ ሬዲዮ ያነጋገራቸው የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወይዘሮ... read more
በኢንዶኔዢያ የመርከብ የእሳት አደጋ ሦስት ሰዎች ሲሞቱ ከ500 በላይ ተሳፋሪዎች ወደ ባህር በመዝለል ሕይወታቸውን አተረፉ
ሐምሌ 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በኢንዶኔዢያ ሱላዌሲ የባህር ዳርቻ ላይ አንድ ጀልባ በእሳት ከተያያዘ በኋላ ሦስት ሰዎች ሲሞቱ፣ ከ500 በላይ... read more
የእስራኤል እና የኢራን ጦርነት አሁናዊ ሁኔታ
ባለፉት ቀናት በእስራኤል እና በኢራን መካከል ያለው ግጭት እጅግ በጣም ተባብሶ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የከተተ ክስተቶች ተከስተዋል። ሁለቱም ሀገራት በቀጥታ... read more
በሞርጋን ሮጀርስ የዝውውር ኡደት በማንቸስተር ዩናይትድ መቀደማቸውን የተረዱት አርሰናሎች፣ ፊታቸውን ወደ ሞርጋን ጊብስ-ዋይት ማዞራቸውን የሚጠቁሙ መረጃዎች ወጥተዋል
ሰኔ 01 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) አርሰናል የአጥቂ መስመሩን ለማጠናከር የኖቲንግሃም ፎረስቱን የጨዋታ አቀጣጣይ ሞርጋን ጊብስ-ዋይትን ለማስፈረም ፍላጎት አሳይቷል፤ ሆኖም ተጫዋቹን... read more
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ እንደ ኢጋድ ያሉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ታዛቢ ሆነው እንደሚሳተፉና 1 ሺህ 1 መቶ 31 የሚሆኑ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችም ዘገባ ለማቅረብ ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተገለጸ
ሚያዚያ 16 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ተጠባቂው ሰባተኛው አገራዊ ምርጫ ከአገር ውስጥ ባለፈ የውጭ ታዛቢዎች የሚሳተፉበት መሆኑ ተመልክቷል።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ... read more
የአርበኞች ቀንና የኋላ ታሪካቸው
👉
https://youtu.be/8PGo7h-L6zU
read more
የአሜሪካ የኑክሌር ሚስጥር በዲጂታል ካርዶች አማካኝነት ለዓለም ተጋለጠ!
ሚያዚያ 15 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ባለፈው የፈረንጆች አመት ቤሊንግካት (Bellingcat) የተባለው የምርመራ ተቋም ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት የአሜሪካ አየር ሃይል አባላት... read more
የህጻናት ፍትህ የማግኘት መብት ተገቢ ትኩረት እያገኘ አለመሆኑ እንዳሳሰበው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጸ
ህጻናት ለሚገባቸው ፍትህ ተገቢውን ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ረገድ የሚመለከታቸው አካላት በቅጡ እየሰሩ እንዳልሆነ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ለመናኸሪያ ሬዲዮ አስታውቋል።
ዛሬም... read more
በጃካርታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መስጊድ ውስጥ በተከታታይ ፍንዳታዎች ቢያንስ 54 ሰዎች ቆሰሉ
ጥቅምት 28 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በኢንዶኔዥያ ዋና ከተማ ጃካርታ በሚገኝ አንድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መስጊድ ውስጥ ባልታወቀ... read more
ለሀገራዊ ምክክሩ ጉባኤ አጀንዳዎች ተለይተው መቅረባቸው ለውይይቱ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ
ሰኔ 19 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን መሠረታዊ ችግሮች በምክክር ለመፍታት ስታደርገው የነበረው ጥረት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ይታወቃል።
ሀገራዊ የምክክር... read more
ምላሽ ይስጡ