ሐምሌ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአትሌቲኮ ማድሪድ ክለብ የፖርቹጋሉን ስፖርቲንግ ሊዝበን አምበል እና የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን አማካኝ ሞርተን ዩልማንድን ለማስፈረም የተቃረበ ሲሆን፣ በግል ጥቅማጥቅሞች ዙሪያ ከተጫዋቹ ጋር ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ማትዮ ሞሬቶ እንደዘገበው፤ አትሌቲኮ ማድሪድ ከሊዝበን ጋር የነበረው የ35 ሚሊዮን ዩሮ የመጀመሪያ ጥያቄ ውድቅ ከተደረገበት በኋላ፣ አጠቃላይ የዝውውር ሂሳቡን ወደ 40 ሚሊዮን ዩሮ (35 ሚሊዮን ቋሚ እና 5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ማበረታቻዎች) በማሳደግ ተጫዋቹን ለማስፈረም ተቃርቧል።
የ26 ዓመቱ አማካኝ እስከ 2031 ዓ.ም የሚያቆየውን የ5 ዓመት ኮንትራት ለመፈረም የተስማማ ሲሆን፣ በአዲሱ ክለቡ የቅድመ-ውድድር ዝግጅት ለመጀመር ወደ ማድሪድ ያመራል ተብሎ ይጠበቃል። አትሌቲኮ ማድሪድ ፊቱን ወደ ዩልማንድ ያዞረው፣ ከዎልቭሱ ጆአኦ ጎሜስ ወኪል ጆርጅ ሜንዴስ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ተከትሎ የዝውውር እቅዱን በመቀየሩ ነው።
ሞርተን ዩልማንድ ባለፈው የ2025/2026 የውድድር ዘመን በፖርቹጋል ፕሪሜራ ሊጋ እና በተለያዩ ውድድሮች ለስፖርቲንግ ሊዝበን በአማካኝ መስመር ላይ ቁልፍ ሚና የነበረው ሲሆን፣ 1 ግብ አስቆጥሮ 1 ለግብ የሚሆን ኳስ ማመቻቸት ችሏል።
አትሌቲኮ ማድሪድ ይህንን ተጫዋች አጥብቆ የፈለገበት ዋነኛው ምክንያት በአሰልጣኝ ዲዬጎ ሲሚዮኒ የጨዋታ ስልት ውስጥ ጠንካራ፣ ኳስ አስጣይ እና መከላከል ላይ ያተኮረ ንቁ የተከላካይ አማካኝ (Defensive Midfielder) እንዲሁም በተከላካይ እና በአጥቂ መስመር መካከል ድልድይ የሚሆን ተጫዋች ስለሚያስፈልገው ነው።
ዩልማንድ በስፖርቲንግ ሊዝበን መሪነቱን እና የአማካኝ ክፍሉን በአግባቡ የመቆጣጠር ብቃቱን ያሳየ በመሆኑ፣ ሲሚዮኒ ለሚገነቡት አዲስ የአማካኝ መስመር ጥንካሬ ዋነኛ ምርጫቸው አድርገውታል፤ ተጫዋቹም በሮጂብላንኮዎቹ ቤት ለ5 ዓመታት የሚያቆየውን ኮንትራት ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ኢጋድ የአንካራውን ስምምነት እንደሚደግፍ ገለጸ
ታኅሳስ 03 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መንግስት መካከል የተደረሰውን ስምምነት እንደሚደግፍ አስታወቀ።
ስምምነቱን... read more
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋፋት ንቅናቄ ማስጀመሩን ይፋ አደረገ
ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ “አካታች የባንክ አገልግሎት ለሁሉም!” በሚል መሪ ቃል፤ ከሰኔ 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት... read more
ግማሽ ጭንቅላቷን ብታጣም ተስፋ አልቆረጠችም፦ የክሪስቲና ሳንታውስ አስገራሚ የሕይወት ታሪክ
መጋቢት 08 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በስምንት ዓመቷ ሕይወቷን አደጋ ላይ የሚጥልና በቀን እስከ 150 ጊዜ የሚደርስ የሚጥል በሽታ (seizure) ያጋጥማት... read more
ሲፈን ሀሰን በሳምንቱ መጨረሻ በሚደረገው የሲድኒ ማራቶን የማሸነፍ ቅድሚያ ግምቱን አገኘች
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፈን ሀሰን በመጪው መስከረም ወር ላይ በሀገረ ጃፓን ቶኪዮ ከተማ ላይ በሚከናወነው... read more
ቤተሰብን ለመደገፍ በሚሰራው ስራ የመዋቅርና የፖሊሲ ማዕቀፍ ችግር መኖሩ ተገለጸ
ቤተሰብን በመደገፍ ስራ ውስጥ የመዋቅርና የፖሊሲ ማዕቀፍ ችግር መኖሩን ለጣቢያችን የገለጸው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው።
ኢትዮጵያ አለም አቀፍ የቤተሰብ ህጎችን... read more
ለሰብዓዊ ድጋፍ የሚወል ከ100 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በሰብል መሸፈኑን የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ
ኅዳር 25 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በየጊዜዉ በሚከሰቱ ሰዉ ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ምክንያት የተረጂ ዜጎች ቁጥር መጨመሩ ይገለጻል፡፡
በዚህም ምክንያት ከቤት... read more
የአካል ጉዳተኞችን የስራ እና የገበያ ትስስር ችግር በከፍተኛ ሁኔታ ይቀርፋል የተባለ የዲጂታል ስልጠና ስርዓተ ትምህርት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ሊሰጥ መሆኑ ተገለጸ
አካል ጉዳተኞች ምርት እና አገልግሎቶቻቸውን በማስተዋወቅ እና ለገበያ በማቅረብ ሒደት የሚገጠሟቸውን ችግሮች መቅረፍ የሚስያችል የዲጂታል ስልጠና ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ በቴክኒክና... read more
የብሔር ብሔረሰቦች የዘመን መለወጫ እንደ ካላንደር መታየት የለበትም ተባለ
https://youtu.be/k43lj7ZNPrw
read more
የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተሰጠውን ጊዜ በአግባቡ አልተጠቀመም ሲሉ የምክር ቤት አባላት ገለፁ
በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ3 ዓመት የስራ... read more
ምላሽ ይስጡ