ሐምሌ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአትሌቲኮ ማድሪድ ክለብ የፖርቹጋሉን ስፖርቲንግ ሊዝበን አምበል እና የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን አማካኝ ሞርተን ዩልማንድን ለማስፈረም የተቃረበ ሲሆን፣ በግል ጥቅማጥቅሞች ዙሪያ ከተጫዋቹ ጋር ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ማትዮ ሞሬቶ እንደዘገበው፤ አትሌቲኮ ማድሪድ ከሊዝበን ጋር የነበረው የ35 ሚሊዮን ዩሮ የመጀመሪያ ጥያቄ ውድቅ ከተደረገበት በኋላ፣ አጠቃላይ የዝውውር ሂሳቡን ወደ 40 ሚሊዮን ዩሮ (35 ሚሊዮን ቋሚ እና 5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ማበረታቻዎች) በማሳደግ ተጫዋቹን ለማስፈረም ተቃርቧል።
የ26 ዓመቱ አማካኝ እስከ 2031 ዓ.ም የሚያቆየውን የ5 ዓመት ኮንትራት ለመፈረም የተስማማ ሲሆን፣ በአዲሱ ክለቡ የቅድመ-ውድድር ዝግጅት ለመጀመር ወደ ማድሪድ ያመራል ተብሎ ይጠበቃል። አትሌቲኮ ማድሪድ ፊቱን ወደ ዩልማንድ ያዞረው፣ ከዎልቭሱ ጆአኦ ጎሜስ ወኪል ጆርጅ ሜንዴስ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ተከትሎ የዝውውር እቅዱን በመቀየሩ ነው።
ሞርተን ዩልማንድ ባለፈው የ2025/2026 የውድድር ዘመን በፖርቹጋል ፕሪሜራ ሊጋ እና በተለያዩ ውድድሮች ለስፖርቲንግ ሊዝበን በአማካኝ መስመር ላይ ቁልፍ ሚና የነበረው ሲሆን፣ 1 ግብ አስቆጥሮ 1 ለግብ የሚሆን ኳስ ማመቻቸት ችሏል።
አትሌቲኮ ማድሪድ ይህንን ተጫዋች አጥብቆ የፈለገበት ዋነኛው ምክንያት በአሰልጣኝ ዲዬጎ ሲሚዮኒ የጨዋታ ስልት ውስጥ ጠንካራ፣ ኳስ አስጣይ እና መከላከል ላይ ያተኮረ ንቁ የተከላካይ አማካኝ (Defensive Midfielder) እንዲሁም በተከላካይ እና በአጥቂ መስመር መካከል ድልድይ የሚሆን ተጫዋች ስለሚያስፈልገው ነው።
ዩልማንድ በስፖርቲንግ ሊዝበን መሪነቱን እና የአማካኝ ክፍሉን በአግባቡ የመቆጣጠር ብቃቱን ያሳየ በመሆኑ፣ ሲሚዮኒ ለሚገነቡት አዲስ የአማካኝ መስመር ጥንካሬ ዋነኛ ምርጫቸው አድርገውታል፤ ተጫዋቹም በሮጂብላንኮዎቹ ቤት ለ5 ዓመታት የሚያቆየውን ኮንትራት ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ጥምረት ወደ ውህደት ሊያድግ እንደሚችል ቢገለጽም የፓርቲዎቹ ቅድመ ስምምነት ግን ያላለቀ የቤት ስራ መሆኑ ተገለጸ
ነሐሴ 14 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) የአስራ አንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥምረት ይፋ መደረጉን ተከትሎ ጥምረቱ ወደ ውህደትም የሚያድግ መሆኑ ተገልጿል።
አሁን... read more
በትግራይ ክልል የሚገኙ የጸጥታ ሃይሎች ወደ ጦርነት እንዳይገቡ ቅስቀሳ እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
ሐምሌ 28 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል የሚገኙ የጸጥታ ሃይሎች በተለያዩ ምክንያቶች ተገፋፍተው ወደ ጦርነት እንዳይገቡ ቅስቀሳ እያደረገ መሆኑን ስምረት... read more
በኢትዮጵያ የግብርና ምርት ብክነትና የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተግዳሮቶች
ግብርና የበርካታ አገራትን ምጣኔ ሃብታዊ እንቅስቃሴ ያሳደገ፣ ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር በፍጥነት እንዲሸጋገሩ ያደረገ መሆኑ ይታወቃል። እንደ ቻይና፣ አሜሪካ... read more
በአድዋ ድል የተገኘውን የአሸናፊነት ስነ ልቦና አሁን ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት መጠቀም ይገባል ተባለ
አድዋ ከፍተኛ የሃገር ፍቅር ስሜት የታየበት የመላው ጥቁር ህዝቦች ድል መሆኑ ይታወቃል።
በአድዋ ጦርነት የታየው የአሸናፊነት እና የይቻላል እሳቤ ትልቅ ትሩፋት... read more
ሰበር ዜና፡ ከሰሜን ኮሪያ የተተኮሰው ሚሳኤል የቀጣናውን ውጥረት እንደገና አናጋው!
ነሐሴ 06 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)አሜሪካ እና ደቡብ ኮሪያ ሊያካሂዱት ካዘጋጁት ግዙፍ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ፣ ሰሜን... read more
አካታች የትምህርት ፖሊሲዎች በወረቀት ላይ ቢኖሩም በተግባር እየተሰራባቸው አለመሆኑ ተገለጸ
ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) አብርሆት ስፔሻላይዝድ የሳይኮሎጂ ማዕከል ከለርኒንግ ሊንክ አፍሪካ፣ ከኬንያታ ዩኒቨርሲቲ፣ እንዲሁም ከሌሎች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር... read more
በጋምቤላ ክልል ህጻናት በቤት እንስሳት እየተለወጡ ነው ተባለ
በጋምቤላ ክልል ህጻናትን በቤት እንስሳት የመለዋወጡ ልማድ አሁንም ድረስ አለመቀረፉ እንዳሳሰበው የገለጸው የክልሉ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ነው፡፡
ቢሮው አሁንም... read more
በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ሃይል ተጠቃሚ ለሆኑ ደንበኞች ሙሉ ለሙሉ የስማርት ቆጣሪ ገጠማ መደረጉ ተገለጸ
የከፍተኛ ሃይል ተጠቃሚ ለሆኑ ደንበኞች የቆጣሪ ቅያሪ ለማድረግ እቅድ ተይዞ ሲሰራ መቆየቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመናኸሪያ ሬዲዮ አስታውቋል፡፡
በዚህም መሰረት በሀገሪቱ... read more
አማርኛ ቋንቋን የአፍሪካ ህብረት የስራ ቋንቋ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶች አሁንም መቀጠል እንዳለባቸዉ ተጠቆመ
38ኛዉ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ በመጪዉ ቅዳሜና እሁድ እንደሚካሄድ ይታወቃል፡፡
ህብረቱ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ አጀንዳዎችን በማንሳት በጉባዔው ካሉ የህብረቱ መሪዎችን የማወያየት... read more
በረቂቅ አዋጁ እጩዎች 3ሺሕ ፊርማ እንዲያቀርቡ የሚጠይቀው ድንጋጌ ተሻሽሎ አለመቅረቡ ቅሬታ አስነሳ
ሐምሌ 07 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ምርጫ ቦርድ በስራ ላይ የሚገኘው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና ስነ ምግባር አዋጅ 1162/2011 ላይ ማሻሻያ በማድረግ ለውይይት... read more
ምላሽ ይስጡ