ሐምሌ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአትሌቲኮ ማድሪድ ክለብ የፖርቹጋሉን ስፖርቲንግ ሊዝበን አምበል እና የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን አማካኝ ሞርተን ዩልማንድን ለማስፈረም የተቃረበ ሲሆን፣ በግል ጥቅማጥቅሞች ዙሪያ ከተጫዋቹ ጋር ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ማትዮ ሞሬቶ እንደዘገበው፤ አትሌቲኮ ማድሪድ ከሊዝበን ጋር የነበረው የ35 ሚሊዮን ዩሮ የመጀመሪያ ጥያቄ ውድቅ ከተደረገበት በኋላ፣ አጠቃላይ የዝውውር ሂሳቡን ወደ 40 ሚሊዮን ዩሮ (35 ሚሊዮን ቋሚ እና 5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ማበረታቻዎች) በማሳደግ ተጫዋቹን ለማስፈረም ተቃርቧል።
የ26 ዓመቱ አማካኝ እስከ 2031 ዓ.ም የሚያቆየውን የ5 ዓመት ኮንትራት ለመፈረም የተስማማ ሲሆን፣ በአዲሱ ክለቡ የቅድመ-ውድድር ዝግጅት ለመጀመር ወደ ማድሪድ ያመራል ተብሎ ይጠበቃል። አትሌቲኮ ማድሪድ ፊቱን ወደ ዩልማንድ ያዞረው፣ ከዎልቭሱ ጆአኦ ጎሜስ ወኪል ጆርጅ ሜንዴስ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ተከትሎ የዝውውር እቅዱን በመቀየሩ ነው።
ሞርተን ዩልማንድ ባለፈው የ2025/2026 የውድድር ዘመን በፖርቹጋል ፕሪሜራ ሊጋ እና በተለያዩ ውድድሮች ለስፖርቲንግ ሊዝበን በአማካኝ መስመር ላይ ቁልፍ ሚና የነበረው ሲሆን፣ 1 ግብ አስቆጥሮ 1 ለግብ የሚሆን ኳስ ማመቻቸት ችሏል።
አትሌቲኮ ማድሪድ ይህንን ተጫዋች አጥብቆ የፈለገበት ዋነኛው ምክንያት በአሰልጣኝ ዲዬጎ ሲሚዮኒ የጨዋታ ስልት ውስጥ ጠንካራ፣ ኳስ አስጣይ እና መከላከል ላይ ያተኮረ ንቁ የተከላካይ አማካኝ (Defensive Midfielder) እንዲሁም በተከላካይ እና በአጥቂ መስመር መካከል ድልድይ የሚሆን ተጫዋች ስለሚያስፈልገው ነው።
ዩልማንድ በስፖርቲንግ ሊዝበን መሪነቱን እና የአማካኝ ክፍሉን በአግባቡ የመቆጣጠር ብቃቱን ያሳየ በመሆኑ፣ ሲሚዮኒ ለሚገነቡት አዲስ የአማካኝ መስመር ጥንካሬ ዋነኛ ምርጫቸው አድርገውታል፤ ተጫዋቹም በሮጂብላንኮዎቹ ቤት ለ5 ዓመታት የሚያቆየውን ኮንትራት ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ከግማሽ በላይ የሚሆነው የወርቅ ምንጭ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነው ተባለ
ሐምሌ 15 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በምድር ላይ ከዘመናት ሁሉ ከተመረተው ወርቅ ግማሽ ያህሉ ወይም ከዚያ በላይ የሚሆነው የተገኘው ከአንድ ቦታ ነው... read more
ዘመናዊ የመንገድ ደህንነት ባለመኖሩ አካል ጉዳተኞች ለትራፊክ አደጋ እየተጋለጡ ነው ተባለ
ሰኔ 30 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች ዘመናዊ የመንገድ ግንባታ እየተሰራ ቢሆንም፣ አካል ጉዳተኞችን ያማከለ አለመሆኑን... read more
በኳታር በሚገኘው የአሜሪካ የአየር ማዕከል ቁልፍ የኮሙዩኒኬሽን ጉልላት በኢራን ሚሳኤል ጥቃት ወደመ
ሐምሌ 05 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት እየጨመረ ባለበት ወቅት፣ በኳታር አል ዑዴይድ በሚገኘው የአሜሪካ አየር ማዕከል ላይ ኢራን ባደረሰችው... read more
የአጥንት ጤና ለጭንቅላት ንቃትና ለትውስታ ያለውን ወሳኝ ሚና ተመራማሪዎች ይፋ አደረጉ
ግንቦት 06 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) አጥንቶቻችን የሰውነታችንን ቅርፅ ከመያዝ ባለፈ እንደ ልብ እና ሳንባ ሁሉ ንቁ የሆርሞን አመንጪ አካል መሆናቸው... read more
የኢትዮጵያ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናት በሚቀጥሉት 4 ወራት እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ
በተያዘው አመት መስከረም ወር ላይ የተጀመረው የስነ-ህዝብና ጤና ቆጠራ ባለፉት 8 ወራት ውስጥ በሁሉም የሃገሪቱ ክልሎች በተሰራው ስራ ከግማሽ በላይ... read more
ጊፍት ሪል እስቴት 2 ሺሕ ቤቶችን ለመሸጥ የሚያስችለውን የሽያጭ መርሃ ግብር በይፋ አስጀመረ
ነሐሴ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ጊፍት ሪል እስቴት በለገሀር ሳይቱ 2 ሺሕ ቤቶችን ለሽያጭ ማቅረቡን በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል።
ከ2ሺህ ቤቶቹ... read more
በመቀሌ ከተማ ከ15ሺ ሊትር በላይ ነዳጅ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወረ መያዙ ተገለጸ
ባለፉት 15 ቀናት ምንም አይነት ነዳጅ ወደ ክልሉ አለመግባቱን ያስታወቀው የትግራይ ክልል የንግድና ሸማቾች ጥበቃ ቢሮ፣ በመቀሌ ከተማ በህገ... read more
ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ከሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ተገለጸ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ከሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢ/ር ዋሊድ ቢን አብዱልከሪም ኤልኬሬጂ ጋር በጽ/ቤታቸው... read more
የፍሳሽ አወጋገድን በተመለከተ የወጣው መመሪያ አቅመ ደካሞችን ያማከለ አይደለም ተባለ
👉የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በበኩሉ የዜጎችን ህገ-መንግስታዊ መብት ያስጠበቀ መመሪያ ነው ብሏል።
ሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)ቅሬታቸውን... read more
ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ በሚንቀሳቀሱ የቀይ መስቀል አባላት እና ንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርሱ አካላት ከድርጊታቸዉ እንዲቆጠቡ ተጠየቀ
ታኅሳስ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የቀይ መስቀል ማህበር ከተቋቋመበት ከ1927 ዓ.ም ጀምሮ የተለያዩ ሰብዓዊ ድጋፎች እና የልማት ተግባራትን እያከናወነ የሚገኝ... read more
ምላሽ ይስጡ