ሐምሌ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአትሌቲኮ ማድሪድ ክለብ የፖርቹጋሉን ስፖርቲንግ ሊዝበን አምበል እና የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን አማካኝ ሞርተን ዩልማንድን ለማስፈረም የተቃረበ ሲሆን፣ በግል ጥቅማጥቅሞች ዙሪያ ከተጫዋቹ ጋር ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ማትዮ ሞሬቶ እንደዘገበው፤ አትሌቲኮ ማድሪድ ከሊዝበን ጋር የነበረው የ35 ሚሊዮን ዩሮ የመጀመሪያ ጥያቄ ውድቅ ከተደረገበት በኋላ፣ አጠቃላይ የዝውውር ሂሳቡን ወደ 40 ሚሊዮን ዩሮ (35 ሚሊዮን ቋሚ እና 5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ማበረታቻዎች) በማሳደግ ተጫዋቹን ለማስፈረም ተቃርቧል።
የ26 ዓመቱ አማካኝ እስከ 2031 ዓ.ም የሚያቆየውን የ5 ዓመት ኮንትራት ለመፈረም የተስማማ ሲሆን፣ በአዲሱ ክለቡ የቅድመ-ውድድር ዝግጅት ለመጀመር ወደ ማድሪድ ያመራል ተብሎ ይጠበቃል። አትሌቲኮ ማድሪድ ፊቱን ወደ ዩልማንድ ያዞረው፣ ከዎልቭሱ ጆአኦ ጎሜስ ወኪል ጆርጅ ሜንዴስ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ተከትሎ የዝውውር እቅዱን በመቀየሩ ነው።
ሞርተን ዩልማንድ ባለፈው የ2025/2026 የውድድር ዘመን በፖርቹጋል ፕሪሜራ ሊጋ እና በተለያዩ ውድድሮች ለስፖርቲንግ ሊዝበን በአማካኝ መስመር ላይ ቁልፍ ሚና የነበረው ሲሆን፣ 1 ግብ አስቆጥሮ 1 ለግብ የሚሆን ኳስ ማመቻቸት ችሏል።
አትሌቲኮ ማድሪድ ይህንን ተጫዋች አጥብቆ የፈለገበት ዋነኛው ምክንያት በአሰልጣኝ ዲዬጎ ሲሚዮኒ የጨዋታ ስልት ውስጥ ጠንካራ፣ ኳስ አስጣይ እና መከላከል ላይ ያተኮረ ንቁ የተከላካይ አማካኝ (Defensive Midfielder) እንዲሁም በተከላካይ እና በአጥቂ መስመር መካከል ድልድይ የሚሆን ተጫዋች ስለሚያስፈልገው ነው።
ዩልማንድ በስፖርቲንግ ሊዝበን መሪነቱን እና የአማካኝ ክፍሉን በአግባቡ የመቆጣጠር ብቃቱን ያሳየ በመሆኑ፣ ሲሚዮኒ ለሚገነቡት አዲስ የአማካኝ መስመር ጥንካሬ ዋነኛ ምርጫቸው አድርገውታል፤ ተጫዋቹም በሮጂብላንኮዎቹ ቤት ለ5 ዓመታት የሚያቆየውን ኮንትራት ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
☕️ቡና፡ የተፈጥሮ የእርጅና መከላከያ ሊሆን እንደሚችል ጥናት አመላከተ
ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የጥዋት ቡናዎ ከእንቅልፍ የመቀስቀሻ ብቻ ሳይሆን በየቀኑ የሚወስዱት የእርጅና መከላከያ ሊሆን እንደሚችል አዲስ ጥናት አመልክቷል።
ከለንደን የንግስት... read more
ሩሲያ የድሮን ስጋትን የሚቀይር አዲስ ጥይት ሰራች
👉ከአውቶማቲክ ጠመንጃ ሲተኮስ ወደ ሦስት ተከፍሎ ድሮኖችን የሚያሳድደው “ምኖጎቶቺዬ” በጦር ሜዳ ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው! ሐምሌ 03 ቀን... read more
በትግራይ ክልል አሁን ላይ የተከለከለ የአደባባይ ሰልፍ የለም ተባለ
ታኅሳስ 02 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በመቀለ ከተማ አጠቃላይ የአደባባይ ሰልፍ እንዳይደረግ የሚል ክልከላ ወጥቷል መባሉን ተከትሎ መናኸሪያ ሬዲዮ ስለ ጉዳዩ... read more
28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ተጭበርበሩ
28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር መጭበርበራቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የገንዘብ ደህንነት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡
የባንኩ ሪፖርት... read more
የፈተና ሂደቱን በሚያውኩ ተማሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ተገለጸ
ዘንድሮ ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8/2017 ዓ/ም የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና 608 ሺህ ተማሪዎች እንደሚወስዱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች... read more
በአሳማ ስጋ መመገብ ምክንያት የተከሰተው ወረርሽኝ እስከ 40 ሺሕ ኢትዮጵያዊያንን ቀጥፎ አልፏል // የህዳር ሲታጠን ሚስጢር
https://youtu.be/X60MwJISe2k
read more
ውስጣዊ የሰላም ችግር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች መቀያየር የዲፕሎማሲው ዘርፍ ተግዳሮቶች እንደነበሩ ተገለጸ
ኅዳር 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ባለፉት 5 ዓመታት ሀገር ውስጥ ያሉ ግጨቶችና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች መቀያየር ተቋሙ ውጤታማ እንዳይሆን እንዳደረገው... read more
የአሜሪካው 82ኛው የአየር ወለድ ክፍለ ጦር ወደ መካከለኛው ምስራቅ ለመዝመት በተጠንቀቅ ላይ መሆኑ ተገለጸ
መጋቢት 16 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታገን) በዓለም ላይ በፈጣን ደራሽነቱ የሚታወቀው 82ኛው የአየር ወለድ ክፍለ ጦር (82nd... read more
ኢሰመኮ ለአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚቀርብላቸው ድጋፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱን ቢገለጽም ቅሬታዎች አልደረሱኝም ሲል የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ
ኅዳር 17 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ለአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚቀርብላቸው ድጋፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ በመጠንም ሆነ... read more
የፍልሰት ሰንሰለት እና የዜማ ፈውስ፤ በኢትዮጵያ በሰው መነገድ እና ሰዎችን በሕገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገርን ለመግታት የሚደረግ የኅብረት ጥረት
በአዲስ አበባ ከተማ የላፍቶ ሰማይ ሥር በሚገኝ አንድ አነስተኛ ቢሮ ውስጥ የሚሰማው የፒያኖ ድምፅ ተራ የሙዚቃ ዜማ አይደለም። ያ ድምፅ... read more
ምላሽ ይስጡ