በአውሮፓ እግር ኳስ ውስጥ ካሉ እጅግ ተስፋ ሰጪ ወጣት ተሰጥኦዎች አንዱ ተደርጎ የሚወሰደው ኬንዳ፥ ባለፈው የውድድር ዓመት ስፖርቲንግ ሊዝበን የፖርቱጋል ሊግ እና የካፕ ዋንጫዎችን በአንድ ላይ እንዲያሳኩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን የ2025 የሊጉ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ተብሎ መመረጡም ይታወሳል። ባለፉት ሁለት የውድድር ዓመታት በክንፍ ማጥቃትም ሆነ በክንፍ ተከላካይነት (wing-back) ሥፍራዎች ላይ በቋሚነት ሲሰለፍ የቆየው ወጣቱ ኮከብ፥ ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ በመምጣቱ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማውና እንደ እሱ ባሉ ወጣቶች ላይ እምነት ከጣለው ክለብ እና ከአሰልጣኝ ሻቢ አሎንሶ ጋር ለመሥራት በጉጉት እንደሚጠብቅ ገልጿል።
ጆቫኒ ኬንዳ በስፖርቲንግ ሊዝበን ታሪክ በመጀመሪያው የውድድር ዓመት ግብ ያስቆጠረ ትንሹ ወጣት ተጫዋች መሆን የቻለ ሲሆን፥ በዚያው ዓመት በሁሉም ውድድሮች 54 ጨዋታዎችን በማድረግ አስደናቂ ታሪክ አስመዝግቧል።
በተጨማሪም በታዋቂው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ መድረክ ላይ ግብ ያስቆጠረ ትንሹ ፖርቹጋላዊ ተጫዋች የመሆን ክብረ ወሰንን በብቸኝነት ይዟል። በቅርቡ በፖርቱጋል ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ውስጥ በመጫወት ላይ የሚገኘውና በ2025 የአውሮፓ ሻምፒዮና ላይ የወቅቱ ምርጥ ስብስብ ውስጥ መካተት የቻለው ኬንዳ፥ በቼልሲ ቤት ጠንክሮ በመሥራት ክለቡ ትልልቅ ዋንጫዎችን እንዲያነሳ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
ምላሽ ይስጡ