ሰኔ 23 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የፈረንሳይ መከላከያ ሚኒስቴር የሀገሪቱን የባህር ኃይል ይበልጥ ለማዘመንና ስልታዊ አቅሟን ለማሳደግ የያዘችው ታላቅ እቅድ አካል የሆነችውንና በኑክሌር ኃይል የምትሰራውን ‘ደ ግራስ’ (De Grasse) የተሰኘች እጅግ ዘመናዊ የባህር ሰርጓጅ መርከብ በይፋ መረከቡ ታውቋል።
በቼርቦርግ የባህር ወደብ የተገነባችውና በውሃ ውስጥ እስከ 5 ሺህ 200 ቶን ክብደት የመሸከም አቅም ያላት ይህቺ ሰርጓጅ መርከብ፤ ፈረንሳይ እድሜጠገብ የሆኑትን የ‘ሩቢስ’ (Rubis) ዝርያ መርከቦቿን ለመተካት ከቀረጸችው የስድስት ሰርጓጅ መርከቦች ፕሮግራም መካከል የመጨረሻዋና እጅግ አስፈሪዋ መሆኗ ተነግሯል።
የባህር ላይ ጥቃቶችን፣ የረጅም ርቀት የስለላ ስራዎችንና ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖችን በልዩ ብቃት የመወጣት አቅም ያላት ይህቺ የ‘ባራኩዳ’ (Barracuda) ዝርያ መርከብ፤ ሙሉ በሙሉ በውሃ ውስጥ ተደብቃ ለ270 ቀናት ያህል ያለ ምንም መቆራረጥ ስራዋን ማከናወን የምትችል ሲሆን 65 የቡድን አባላትንም በውስጧ ትይዛለች። ይበልጥ አስፈሪ የሚያደርጋት ደግሞ በውስጧ የታጠቀቻቸው የባህር ላይ ክሩዝ ሚሳኤሎች፣ የ‘F21’ ከባድ ቶርፔዶዎች እና የ‘Exocet SM39’ የፀረ-መርከብ ሚሳኤሎች መሆናቸውን ወታደራዊ ተንታኞች ገልጸዋል።
የፈረንሳይ የመከላከያ ግዥ ኤጀንሲ (DGA) በበላይነት የመራው ይህ የባራኩዳ ፕሮጀክት፤ በድብቅ የመጓዝ (stealth) እና የረጅም ጊዜ ጽናትን ከኑክሌር አቅም ጋር በማጣመር በአሁኑ ወቅት በአውሮፓ ውስጥ ካሉ እጅግ የላቁና አስፈሪ የኑክሌር ጥቃት ሰርጓጅ መርከብ ንድፎች መካከል ቀዳሚው ተደርጎ ተወስዷል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ከገቢ ግብር፣ ታክስና ቀረጥ ጋር ተያይዞ በ2016 በጀት አመት ወደ 309.8 ሚሊዮን ብር ሳይሰበሰብ መቅረቱ ተገለፀ
ሰኔ 17 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2016 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ህጋዊነት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት በዛሬው እለት ለህዝብ... read more
የፌዴራል መንግሥት ባስፈለገ እና በተገደበ ሁኔታ በክልሎች ጣልቃ እንዲገባ የሚያስችለው አዋጅ መጽደቁ የዜጎችን ሰላምና ደህንነትን ለማረጋግጥ ያግዛል ተባለ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 22ኛ መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል መንግሥት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ የወጣ የማሻሻያ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል፡፡
የአዋጁ... read more
የምስጥ ወተት ከላም ወተት እጅግ የላቀ ገንቢነት ያለው ነው ተባለ
👉ሳይንቲስቶች ለሰው ልጅ ፍጆታ እንዲሆን እያጠኑት ነው ተብሏል
ሐምሌ 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በቅርብ ጊዜ የተደረገ ሳይንሳዊ ጥናት እንደሚያመለክተው፣ የአንድ የተወሰነ የምስጥ... read more
ለፌዴራል መንግስት የተፈቀደው ተጨማሪ በጀት ግልፅነት ይጎድለዋል ተባለ
ኅዳር 18 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 6ኛ... read more
እንግሊዝ እና አሜሪካ የኑክሌር ኃይል ፕሮጀክቶችን ለማፋጠን የሚያስችል ስምምነት ሊፈራረሙ ነው
መስከረም 05 ቀን (መናኸሪያ ሬዲዮ) ዩናይትድ ኪንግደም እና ዩናይትድ ስቴትስ በአትላንቲክ ውቅያኖስ በሁለቱም በኩል የኑክሌር ኃይል ማመንጫዎችን ግንባታ የሚያፋጥን ታሪካዊ... read more
ከተማ አስተዳደሩ ለ2018 በጀት ዓመት 14.5 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት መያዙን ተገለጸ
ነሐሴ 19 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኑሮ መጋራት በሚል በተለያዩ ዘርፎች ላይ በቀጥታ 14.5 ቢሊዮን ብር ድጎማ መዘጋጀቱን የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ... read more
ሚዲያዎች በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ያለውን የመረጃ ፍሰት በሰላማዊ መንገድ በማስተዳደር ለህዝቡና ለሃገሪቱ የሚበጁ ዘገባዎችን በሃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በፖለቲካዊ ሁኔታዋ ላይ እያለፈች ባለችው ወሳኝ ጊዜ ሚዲያዎች በሃላፊነት እና በተጠያቂነት መረጃ ማቅረብ እንዳለባቸው ምሁራን ለመናኸሪያ ሬዲዮ... read more
ለሰዎች ጅራት ሰርተው እየገጠሙ ያሉት የጃፓን ሳይንቲስቶች
ነሐሴ 15 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ጃፓን የሚገኙ ሳይንቲስቶች፣ የሰውን ልጅ ሚዛን ለመጠበቅ የሚረዳ፣ የእንስሳትን ጅራት የሚመስል 'ሮቦቲክ ጅራት' በመንደፍ ፈተና... read more
አፍሪካ ቀስ በቀስ እየተሰነጠቀች አዲስ ውቅያኖስ የመፍጠር ሁኔታዋ እየሰፋ ነው ተባለ
ሐምሌ 08 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ለዓመታት የሳይንስ ሊቃውንትን ትኩረት ሲስብ የቆየው የአፍሪካ ቀጣናዊ ለውጥ አዲስ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
አፍሪካ አህጉር ቀስ... read more
ምላሽ ይስጡ