ሰኔ 02 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ተግባራዊ በሆነው አዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ውስጥ የሀገር በቀል እውቀት ከጽሑፍ ያለፈ ለትግበራ የተዘጋጀ አካሄድ የለም ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ጤና መምህር እና በሀገር በቀል እውቀት ዙሪያ ምርምር የሚያደርጉት ፕሮፌሰር መንገሻ አድማሱ ለጣቢያችን ተናግረዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የተጠና ጥናት ቢኖረውም ወደ ትግበራ አልገባም የሚሉት ባለሙያው፣ ሰነድ ማዘጋጀትና መተግበር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ሌሎች ተቋማትም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በአዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ሀገር በቀል እውቀቶችን አካቶ በትምህርት ቤቶች ውስጥ እንዲተገበር ለማስቻል የማስፈጸሚያ ሰነድ እየተዘጋጀ መሆኑን በትምህርት ሚኒስቴር የሀገር በቀል እውቀትና የማህበረሰብ ትስስር ዴስክ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላም አለሙ ለመናኸሪያ ሬዲዮ ተናግረዋል።
ፍኖተ ካርታው መተግበር ከጀመረ ዓመታትን ያስቆጠረ እንደሆነ የተናገሩት ዳይሬክተሯ፣ ነገር ግን የሀገር በቀል እውቀትን አካቶ ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ለማስቻል የሚቀሩ ስራዎች መኖራቸውን አምነዋል።
ዳይሬክተሯ በሚመሩት የሀገር በቀል እውቀትና የማህበረሰብ ትስስር ዴስክ በኩል የማስፈጸሚያ መመሪያ ሰነድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። ይህ ብቻም ሳይሆን አሁን ላይ በካሪኩለም ወይም በስርዓተ ትምህርት ክፍሉም በኩል እንዲሁ የማስፈጸሚያ መመሪያዎች መቀረጻቸውን ገልጸዋል። ስርዓተ ትምህርቱ ሙሉ በሙሉ የሀገር በቀል እውቀትን እንዲያካትት ለማስቻል ነው በቂ ቅድመ ዝግጅት ያስፈለገው ሲሉም አክለው ተናግረዋል።
አዲስ የትምህርት ፍኖተ ካርታ መቅረጽ ያስፈለገው ሀገር በቀል እውቀቶችን ለማካተት እንደሆነ ካሁን ቀደም የትምህርት ሚኒስትሩ መናገራቸው ይታወሳል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት እድል ልዩነት እንዳለ ተገለጸ
መጋቢት 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) እንደ ሀገር ከትምህርት እድል ጋር በተገናኘ ልዩነት መኖሩን የትምህርት ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
ከክልል እስከ ከተማ የትምህርት እድል... read more
ለሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቂ ድጋፍና እገዛ እንደሚያስፈለገው ተገለጸ
ጥር 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በኢትዮጵያ እየተፈጠሩ ያሉ አለመግባበቶችን ለመቅረፍ የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ ስራን እየሰራ ቢሆንም ተጨማሪ አጋዥ እንደሚያስፈልገው... read more
ቀዳማዊት እመቤት ሜላኒያ ትራምፕ የሰላም መልዕክታቸውን ለፕሬዝዳንት ፑቲን ሰጡ
ነሐሴ 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ቀዳማዊት እመቤት ሜላኒያ ትራምፕ በግላቸው የጻፉትን ለሰላም ጥሪ የሚያደርግ ደብዳቤ... read more
አፍሪካ ዉስጥ በጎች እና ፍየሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሰውን አስከፊ ቫይረስ (ፔስቴ ዴስ ፔቲትስ ሩሚናንት)(PPR) ለመዋጋት የፓን አፍሪካን ፕሮግራም ተጀመረ
አዲስ አበባ በጥር ወር መጨረሻና በየካቲት ወር መጀመሪያ ላይ የአፍሪካ ህብረት ታላላቅ ግቦች እና የፓን አፍሪካ አጀንዳዎች ጋር የተጣጣሙ ወሳኝ... read more
መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ከግማሽ ሚሊዮን የሚልቁ ዜጎችን ማስተናገድ የሚችል አዲስ የገና ኤክስፖ ሊከፈት ነው ተባለ
ታኅሳስ 02 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሮበስት ቢዝነስ ግሩፕ እና በሰላሳ መልቲ ሚዲያ አዘጋጅነት፣ ለ24 ቀናት የሚቆይ ሀገር አቀፍ ኤክስፖ ከንግድና... read more
ስጋቱ ተቀጣጥሎ ቀጥሏል
👉
https://youtu.be/D_OV1HZakvU
በትዕግስቱ በቀለ
read more
ባለፉት 6 ወራት ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው ከመጡት ውስጥ 25ሺሕ 581ዱ ብቻ ተገቢውን መስፈርት ያሟሉ መሆናቸውን የሲቭል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ገለጸ
ከክልል ከተሞች መሸኛ ይዘው ከመጡት ውስጥ 25ሺህ 581ዱ ብቻ በመዲናዋ የሚጠየቀውን መስፈርት ያሟሉ መሆናቸውን የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ።
ኤጀንሲው... read more
ጆዜ ሞሪንሆ የሪያል ማድሪድ ቀጣዩ አሰልጣኝ የመሆን እድላቸው እጅግ ሰፊ መሆኑን Sky Sport አረጋግጧል
ግንቦት 04 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ ቡድናቸው ላለፉት ሁለት ዓመታት ያጋጠመው የዋንጫ እጦት በክለቡ ያልተለመደ እና እንግዳ ነገር መሆኑን... read more
በአዲስ አበባ ከተማ የእብድ ዉሻ በሽታ የተገኘባቸዉን ዉሾች የማስወገዱ ስራ በመደኛ ሁኔታ መቀጠሉ ተገለጸ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን የእንስሳት በሽታ መከላከልና ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ የሺዳኛ በላይሁን የእብድ... read more
ቼልሲዎች ከሬናቶ ቬይጋ ጋር በቋሚነት ለመለያየት ዝግጁ ስለመሆናቸው አሳውቀዋል።
ጥር 06 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የዝውውር መስኮቱ ሲከፈት ቼልሲ ሁሉ አማረሽ ይመስል የተጫዋቾች አቅም ፤ ክህሎት ከአሰልጣኙ ፍልስፍና ጋር ተጣጥሞ... read more
ምላሽ ይስጡ