ሰኔ 23 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የፈረንሳይ መከላከያ ሚኒስቴር የሀገሪቱን የባህር ኃይል ይበልጥ ለማዘመንና ስልታዊ አቅሟን ለማሳደግ የያዘችው ታላቅ እቅድ አካል የሆነችውንና በኑክሌር ኃይል የምትሰራውን ‘ደ ግራስ’ (De Grasse) የተሰኘች እጅግ ዘመናዊ የባህር ሰርጓጅ መርከብ በይፋ መረከቡ ታውቋል።
በቼርቦርግ የባህር ወደብ የተገነባችውና በውሃ ውስጥ እስከ 5 ሺህ 200 ቶን ክብደት የመሸከም አቅም ያላት ይህቺ ሰርጓጅ መርከብ፤ ፈረንሳይ እድሜጠገብ የሆኑትን የ‘ሩቢስ’ (Rubis) ዝርያ መርከቦቿን ለመተካት ከቀረጸችው የስድስት ሰርጓጅ መርከቦች ፕሮግራም መካከል የመጨረሻዋና እጅግ አስፈሪዋ መሆኗ ተነግሯል።
የባህር ላይ ጥቃቶችን፣ የረጅም ርቀት የስለላ ስራዎችንና ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖችን በልዩ ብቃት የመወጣት አቅም ያላት ይህቺ የ‘ባራኩዳ’ (Barracuda) ዝርያ መርከብ፤ ሙሉ በሙሉ በውሃ ውስጥ ተደብቃ ለ270 ቀናት ያህል ያለ ምንም መቆራረጥ ስራዋን ማከናወን የምትችል ሲሆን 65 የቡድን አባላትንም በውስጧ ትይዛለች። ይበልጥ አስፈሪ የሚያደርጋት ደግሞ በውስጧ የታጠቀቻቸው የባህር ላይ ክሩዝ ሚሳኤሎች፣ የ‘F21’ ከባድ ቶርፔዶዎች እና የ‘Exocet SM39’ የፀረ-መርከብ ሚሳኤሎች መሆናቸውን ወታደራዊ ተንታኞች ገልጸዋል።
የፈረንሳይ የመከላከያ ግዥ ኤጀንሲ (DGA) በበላይነት የመራው ይህ የባራኩዳ ፕሮጀክት፤ በድብቅ የመጓዝ (stealth) እና የረጅም ጊዜ ጽናትን ከኑክሌር አቅም ጋር በማጣመር በአሁኑ ወቅት በአውሮፓ ውስጥ ካሉ እጅግ የላቁና አስፈሪ የኑክሌር ጥቃት ሰርጓጅ መርከብ ንድፎች መካከል ቀዳሚው ተደርጎ ተወስዷል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በሰዓት ከ55 እስከ 60 የሚደርሱ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል የወባ መመርመሪያ ወደ ኢትዮጵያ ሊገባ መሆኑ ተገለጸ
ነሐሴ 15 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት በየጊዜው በወባ ዙሪያ በርካታ ጥናቶችን በማድረግ ላይ መሆኑን ለመናኸሪያ ሬዲዮ የገለጹት... read more
የተፋሰሱ ሃገራት ኮሚሽን ሊቋቋም ባለበት ወቅት ግብጽ ወደ ናይል ትብብር መመለሷን ኢትዮጵያ በአጽዕኖት መከታተል አለባት ተባለ
የአባይ ውሃን በፍትሀዊነት እና በምክንያታዊነት ለመጠቀም ከ15 ዓመት በፊት የተቋቋመ የናይል ቤዚ ኢንሼቲቭ ህጋዊ ቢሆንም ግብፅ ውድቅ ማድረጓዋ እና የናይል... read more
የፈረንጆች አዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ርችት እንደሚተኮስ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ
ታኅሳስ 22 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የደህንነትና ልዩ ኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ዛሬ ታህሳስ 22 ቀን 2017... read more
ባለፉት 11 ወራት 1ሺሕ 400 በህገ ወጥ ተይዘው የነበሩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለመንግስት ተመላሽ እንዲሆን መደረጉ ተገለጸ
ሰኔ 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 11 ወራት 1ሺሕ 400 የሚሆኑ በህገ ወጥ አካላት ተይዘው የነበሩ የጋራ... read more
የቴኳንዶ ስፖርት በበጀት ችግር ምክንያት የታሰበውን ያህል እያደገ አለመሆኑ ተገለጸ
እንደ ሀገር ህብረተሰቡ እንዲሁም ስፖርቱን ከመንግስት በተጨማሪ ይደግፋሉ ተብለዉ የሚታሰቡ ባለሀብቶች ስለ ቴኳንዶ ስፖርት ግንዛቤው ስለሌላቸው ተደጋጋሚ የበጀት እጥረት እንዲገጥመው... read more
ፕሪሚየር ሊጉ የትኛውም ቡድን የPSr ህግጋቶችን አልጣሰም በሚል የነጥብ ቅጣት እንደማያስተላልፍ አሳውቋል
ጥር 07 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የትርፋማነት እና ይዘት ክፍፍል በተለይ ደግሞ ወጪ እና ገቢያቸውን በማያመጣጥኑ ክለቦች ላይ ፕሪሚየር ሊጉ የነጥብ ቅጣት... read more
በክልል ከተሞች በቤቲንግ ውርርድ ዘርፍ የተሰማሩ ግለሰቦችን መቆጣጠር ባለመቻሉ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች ለችግር እየተጋለጡ ነው ተብሏል
ኅዳር 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ባለፉት ጊዜያት በመዲናዋ በቤቲንግ ውርርድ ዘርፍ የተሰማሩ አካላት ህገ-ወጥ ድርጊትን መቆጣጠር ተችሏል ቢባልም፤ አሁንም ድረስ... read more
የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚፈጠሩ አደጋዎችን አስቀድሞ ለመቆጣጠር የቅድመ መተንበያ መሳሪያዎችን ለማሟላት እየሰራሁ ነዉ አለ
መጋቢት 09 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚፈጠሩ አደጋዎችን አስቀድሞ ለመቆጣጠር የቅድመ መተንበያ መሳሪያዎችን ከአጋር አካላትና... read more
የንግድ ተቋማት ምዝገባ እስከ ቀጣይ ዓመት ሚያዝያ ወር ድረስ እንሚጠናቀቅ ተገለጸ
ሐምሌ 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በገጠር እና በከተማ የሚገኙ መደበኛም ሆነ ኢ-መደበኛ ነጋዴዎች ፣አምራቾች እና ኢንተርፕራይዞች ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ቆጠራ እንደሚደረግ... read more
ዘመናዊ የመንገድ ደህንነት ባለመኖሩ አካል ጉዳተኞች ለትራፊክ አደጋ እየተጋለጡ ነው ተባለ
ሰኔ 30 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች ዘመናዊ የመንገድ ግንባታ እየተሰራ ቢሆንም፣ አካል ጉዳተኞችን ያማከለ አለመሆኑን... read more
ምላሽ ይስጡ