ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ “አካታች የባንክ አገልግሎት ለሁሉም!” በሚል መሪ ቃል፤ ከሰኔ 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ ቆይታ የሚኖረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን የማስፋት ንቅናቄ በዛሬው ዕለት አስጀምሯል።
ሁለተኛው ብሔራዊ የፋይናንስ አካታችነት ስትራቴጂ እንደሚያሳየው፣ በኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ወደ 45 በመቶ ቢያድግም፤ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎትን ሊጠቀም ይችላል ተብሎ ከሚታሰበው የኅብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሆነው 12 በመቶው ብቻ እንደሆነ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ገልጸዋል።
በሀገራችን ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኅብረተሰብ ክፍል፣ ከሃይማኖታዊ ዕሴቶቹ ጋር የሚስማማ የባንክ አገልግሎት ስላልተዘጋጀለትና ተደራሽ ስላልሆነ ከአካታች የባንክ አገልግሎት ርቆ መቆየቱን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። በተለይም የባንክ አገልግሎት ተደራሽነቱ አናሳ መሆን፣ ሴቶች ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተጠቃሚነት በእጅጉ እንዲገለሉ ማድረጉንም አብራርተዋል።
በመሆኑም መንግሥት በኢትዮጵያ የፋይናንስ አካታችነትን እና ተደራሽነትን የሚያጎለብቱ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ያሉት አቶ አቤ ሳኖ፤ ከእነዚህም አንዱ ብሔራዊ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን ለማስፋፋት የሚሠራው ሥራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ንግድ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር በአፋር፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ፣ አማራ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ፣ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ዝቅተኛ በሆነባቸው ከ241 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች እና የገጠር ቀበሌዎች የሚተገበር የንቅናቄ መርሃ ግብር ማስጀመሩን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ አምስት ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎች ስለወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ግንዛቤ የመፍጠር ዓላማን ያነገበ መሆኑም ተነግሯል።
ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ከጀመረበት ጥቅምት 2006 ዓ.ም ጀምሮ፣ በወለድ ምክንያት ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተገልለው የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ወደ መደበኛው የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲገቡ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግስት ጋር እያካሄደችው ያለው ግንኙነት የባህር በር ለማግኘት የተሻለ ዲፕሎማሲያዊ አካሄድ ነው ተባለ
ጥር 06 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ፌዴራል መንግስት ጋር እያካሄደችው ያለው ግንኙነት የባህር በር ለማግኘት የተሻለ ዲፕሎማሲያዊ ሂደት መሆኑን አምባሳደሮችና... read more
አፍሪካ ችግሮችን በመቋቋም ዕድገቷን እንድታፋጥን ዘላቂ የፋይናንስ ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተናግረዋል
46ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ "የማካካሻ ፍትሕ ለአፍሪካውያንና ዘርዓ-አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ... read more
አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች የልዩ ፍላጎት ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ላይ ክፍተቶች እንዳሉባቸው ተገለጸ
ሰኔ 19 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሥነ-አእምሮ ሕክምና ሥራም ሆነ በትምህርት ሂደት ውስጥ “ችግር አለበት” ተብሎ የሚገለል ልጅ ሊኖር እንደማይገባ የገለጹት... read more
38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ ይጀመራል
38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ የሚጀመር ሲሆን ጉባኤው “የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን“ በሚል መሪ ሀሳብ ላይ ትኩረቱን... read more
በትግራይ ክልል የሚገኙ የጸጥታ ሃይሎች ወደ ጦርነት እንዳይገቡ ቅስቀሳ እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
ሐምሌ 28 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል የሚገኙ የጸጥታ ሃይሎች በተለያዩ ምክንያቶች ተገፋፍተው ወደ ጦርነት እንዳይገቡ ቅስቀሳ እያደረገ መሆኑን ስምረት... read more
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተደረገው ግምገማ የተገኘዉ ዉጤት አስደንጋጭ ነዉ ተባለ
ነሐሴ 19 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የትምህርት ሥልጠና ባለስልጣን በአዲስ አበባ በሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከመስከረም 08 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ... read more
በአማራ ክልል ያለው ግጭት ከቀጠለ በርካታ ወገኖች ለአዕምሮ ጤና ችግር ይጋለጣሉ ተባለ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር በአማራ ክልል ከሕወሀት ጦርነት ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያሉ ግጭቶች እና ውጥረቶች በተማሪዎች፣ በሴቶች፣... read more
ወደ ፍጻሜው የደረሰው የጋዛ ተኩስ አቁም ስምምነትና ኔታንያሁ የገጠማቸው የካቢኒያቸው ጫና
https://youtu.be/DTfy1rTwgxI
read more
ስልኩ አልተሰበረም! ከ16,000 ጫማ ከፍታ የወደቀው አይፎን! ✈️
ሕዳር 15 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)አስደናቂው የአላስካ ኤርላይንስ በረራ 1282 ክስተት! ከአደጋው በኋላ መርማሪዎችን ያስገረመ ክስተት ተመዝግቧል።
አውሮፕላኑ ወደ 16,000 ጫማ (5... read more
ምላሽ ይስጡ