ነሐሴ 22 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የዝውውር ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራው ታዋቂው ጋዜጠኛ ፋብሪዚዮ ሮማኖ እንደገለጸው፣ ሁለቱ ክለቦች በ58.4 ሚሊዮን ዩሮ ቋሚ ክፍያ እና በ2 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ አበል በድምሩ 60.4 ሚሊዮን ዩሮ በሚደርስ የዝውውር ዋጋ ተስማምተዋል። አስቶን ቪላ ቀደም ሲል የቀረበለትን የዝውውር ጥያቄ ዝቅተኛ ነው በሚል ውድቅ አድርጎት የነበረ ቢሆንም፣ ረጅም ድርድር ካደረጉ በኋላ አሁን ለዝውውሩ አረንጓዴ መብራት ሰጥቷል። በመሆኑም የ30 ዓመቱ አጥቂ የሕክምና ምርመራውን ለማድረግ እና የመጨረሻውን ፊርማ ለማስቀመጥ በዚሁ ሳምንት ወደ ሳዑዲ አረቢያ እንደሚጓዝ ይጠበቃል። በብሬንትፎርድ ቆይታው በኋላ በ2020 አስቶን ቪላን የተቀላቀለው ዋትኪንስ፣ የክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አግቢ መሆን ችሏል። ባለፈው የውድድር ዘመንም በሁሉም ውድድሮች 21 ግቦችን በማስቆጠር ለክለቡ ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል። አስቶን ቪላ የአጥቂውን መውጣት ተከትሎ የተፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት የቼልሲውን አጥቂ ኒኮላስ ጃክሰንን በ65 ሚሊዮን ፓውንድ ለማስፈር ከስምምነት መድረሱ ተገልጿል፤ አልሂላል በበኩሉ ይህንን የፊት መስመር ተጫዋች በማስፈረም የስብስቡን ጥራት የበለጠ አጠናክሯል።
__ ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
ምላሽ ይስጡ