ሐምሌ 30 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ኢኳዶር፣ ባባሆዮ በተባለች ከተማ የሚገኘው ማርቲን ኢካዛ ሆስፒታል ሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ.ም አንድ ያልተለመደና አሳዛኝ ክስተት አስተናግዷል። እድሜያቸው 76 የሆኑት አያት ቤላ ሞንቶያ በጽኑ ታመው ወደ ሆስፒታሉ ከገቡ በኋላ፣ በወቅቱ በነበሩት ሀኪሞች “ህይወታቸው አልፏል” የሚል ኦፊሴላዊ የሞት ምስክር ወረቀት ተሰጣቸው።
የሞታቸውን ዜና የሰሙት ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው የቀብር ስነ-ስርዓታቸውን ለመፈጸም አስከሬኑን በሬሳ ሳጥን ውስጥ አድርገው ወደ ቀብር ማዘጋጃ ቤት ወሰዱት። ለሰዓታት ያህል የሀዘን ስነ-ስርዓት ሲካሄድ ቆይቶ፣ ከቀብሩ በፊት የሬሳ ሳጥኑን ከፍተው ልብሳቸውን ለመቀየር ሲዘጋጁ ግን ያልተጠበቀ ድንጋጤ ተከሰተ።
የአያት ቤላ ሞንቶያ ልጅ የሆነው ጊልበርት ባልቤራን እንደተናገረው፣ ከሰዓታት ሀዘን በኋላ ከሳጥኑ ውስጥ ደካማ ማንኳኳትና የመተንፈስ ድምፅ መሰማት ጀመረ። ቤተሰቦቻቸው ሳጥኑን በፍጥነት ሲከፍቱ፣ አያት በህይወት ሆነው ግራ እጃቸውን በማንቀሳቀስና አፋቸውን በመክፈት አየር ለማግኘት ሲታገሉ ተመለከቱ።
ይህ ክስተት በወቅቱ በሆስፒታሉ ባለሙያዎች ዘንድ ከፍተኛ መደናገጥን የፈጠረ ሲሆን፣ አያት ወዲያውኑ ወደ ጽኑ ህክምና ክፍል ተመልሰው ኦክስጅን እንዲያገኙ ተደረገ። የህክምና ባለሙያዎች እንደሚሉት አያት የካታሌፕሲ (Catalepsy) ተብሎ በሚጠራ የነርቭ መታወክ ሁኔታ ውስጥ ወድቀው የነበረ ሲሆን፣ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ያለ ሰው የልብ ምቱና የመተንፈስ ፍጥነቱ እጅግ አነስተኛ ከመሆኑ የተነሳ እንደ ሞተ ሰው ተቆጥሮ በስህተት ሊደመደም ይችላል።
ክስተቱን ተከተሎ የኢኳዶር ጤና ሚኒስቴር አያት በስህተት ሞተዋል ተብለው የሞት ምስክር ወረቀት እንዴት ሊሰጣቸው እንደቻለ ለማጣራት ብሔራዊ ኮሚቴ አቋቁሞ ምርመራ ጀምሮ ነበር።
ሆኖም ግን፣ አያት ቤላ ሞንቶያ በጽኑ ህክምና ክፍል ውስጥ ለአንድ ሳምንት ያህል ከቆዩ በኋላ ሰኔ 16 ቀን 2015 ዓ.ም በተከሰተ የstroke ችግር ምክንያት ህይወታቸው ማለፉ በይፋ ተረጋግጧል።
የመጀመሪያው አጋጣሚ ግን በዓለም አቀፍ ደረጃ በህክምና ታሪክ ውስጥ እጅግ አስገራሚና በማህበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ መነጋገሪያ ከሆኑ ክስተቶች አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በሀገሪቱ በተለያዩ የከተማ መግቢያና መውጫ ላይ ለኮቴ የሚከፈለው ክፍያ ከተቋሙ እዉቅና ዉጪ ህጋዊ ሽፋን ተሰጥቶት የሚፈጸም ሕገ-ወጥ ተግባር ነዉ አለ
ታኅሳስ 02 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሕዝብና የጭነት አጓጓዞች በሆኑ ተሽከርካሪዎች በየከተማው የሚሰበሰቡ የኮቴ ክፍያዎች ሕጋዊነት የሌላቸዉ መሆኑንና የብዝበዛ ድርጊት እየተፈፀመ... read more
ያልተጠበቀው ሆነ፤የሃማስ መሪው እና ቤንያሚን ኔታንያሁ ተጨባበጡ
ቴል አቪቭ በጋዛ ሃማስ ላይ የምታደርገውን ጦርነት ለማቆም እና እስረኞችን ለመፍታት እንዲሁም፣ ታጣቂ ቡድኑ ታጋቾችን ለመልቀቅ፣ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ... read more
‘’ዛሬ ብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሊዮ አስራ አራተኛ በቫቲካን ተቀብለውናል። ውይይታችን በሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን ለዓለም ሰላም ያለንን የጋራ አቋምም ተወያይተናል። የትምህርት ተደራሽነትን የማስፋት አስፈላጊነትን በተመለከተም የጋራ ስምምነት ይዘናል።’’
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ(ዶ/ር)__
read more
27ሺሕ 755 ያህል ከክልል መሸኛ ይዘው ለመጡ ተገልጋዮች አገልግሎት መስጠቱን ኤጅንሲው አስታውቋል
ሐምሌ 09 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ከአሁን ቀደም ለበርካታ ጊዜ መሸኛ ይዘው ለሚመጡም ተገልጋዮች አገልግሎቱ ቆሞ የነበረ ቢሆንም በዚህ አመት ከህዳር... read more
የዱር እንስሳትን በህይወት የመነገድ እንቅስቃሴ በመቀዛቀዙ ምክንያት የሚፈለገውን ያህል ገቢ እየተገኘ አለመሆኑ ተገለጸ
በኢትዮጵያ የሚገኙ እና ብርቅዬ ያልሆኑ እንዲሁም የመጥፋት አደጋ ያልተጋረጠባቸውን የዱር እንስሳትን አለም አቀፍ ህግና ደንብን በጠበቀ መልኩ በህይወት ለውጭ ሃገር... read more
ወደ አክሱም ከተማ ጎብኚዎች እየሄዱ አለመሆኑ ተገለጸ
ሰኔ 28 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በዩኒስኮ የተመዘገበው የአክሱም ሀውልትና ሌሎች ጥንታዊ ቅርሶች ለመጎብኘት ወደ አክሱም ከተማ የሚሄዱ ጎብኚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ... read more
የኅብረት ሥራ ማኅበርን ስንዴ ባልተገባ ዋጋ ሽጠዋል የተባሉ አመራሮች በጽኑ እስራት ተቀጡ
የአምቦ የገበሬ ኅብረት ሥራ ማኅበር የስንዴ ምርትን ባልተገባ ዋጋ በመሸጥ ከ4 ሚሊየን ብር በላይ አሳጥተዋል የተባሉ የማኅበሩ አመራሮች በጽኑ እስራት... read more
በትግራይ ክልል በ1 ሺህ 800 ሄክታር መሬት ላይ የዛፍ አንበጣ መንጋ መከሰቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ
በትግራይ ክልል አዲስ መጤ ‹የዛፍ አንበጣ› የተባለ ተምች መከሰቱን እና እስከአሁንም በ1 ሺህ 800 ሄክትር መሬት ላይ እንደተሰራጨ በግብርና ሚኒስቴር... read more
ትራምፕ ለታይዋን የሚሰጠውን 400 ሚሊዮን ዶላር ወታደራዊ እርዳታ አገዱ
መስከረም 09 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይና ጋር የንግድ ስምምነት ለማድረግ እና የመሪዎች ስብሰባ ለማዘጋጀት እየሞከሩ በመሆናቸው ለታይዋን የሚሰጠውን... read more
21 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ቤት እየተጓጓዘ ነው – ግብርና ሚኒስቴር
ሰኔ 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በ2017/18 ዓ.ም የመኸር ወቅት የሚውል 21 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ቤት እየተጓጓዘ እንደሚገኝ ግብርና... read more
ምላሽ ይስጡ