ሰኔ 02 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኤክስ (X) ባለቤትና ታዋቂው ቢሊየነር ኢሎን ማስክ በስትራቴጂካዊው የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ስያሜ ዙሪያ በገጹ ላይ ያሰፈረው ታሪካዊ ትንታኔ እና የቋንቋ አጠቃቀም ስህተት ዓለም አቀፍ መነጋገሪያ ሆኗል።
ኢሎን ማስክ ትናንት በይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ ባስተላለፈው አጭር መልዕክት፥ “የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤዎች (Straits of Hormuz) ስያሜያቸውን ያገኙት በዞራስትሪያኒዝም እምነት ውስጥ ‘አሁራ ማዝዳ’ ከተባለው ዋነኛ አምላክ ነው” የሚል የራሱን ታሪካዊ ምልከታ አጋርቶ ነበር። ይህ የቢሊየነሩ ፅሁፍ በአጭር ሰዓታት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ትኩረት የሳበ ቢሆንም፣ ከኢራን መንግስት ወገን ግን ጠንከር ያለ ምላሽ አስተናግዷል።
በህንድ ሙምባይ የሚገኘው የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት የኢሎን ማስክን ስህተት በይፋዊ ገጹ ላይ በግልጽ በማረም ምላሽ የሰጠ ሲሆን፥ “ኢሎን፤ ጥሩ ጅምር ነው፤ ነገር ግን ተጨማሪ ትምህርት ያስፈልግሃል” ሲል በይፋ አፌዝበታል።
ቆንስላው በማስተካከያው ላይ እንደገለጸው፥ በመጀመሪያ ደረጃ ማስክ የተጠቀመው “Straits” (ባህረ ሰላጤዎች) የሚለው የብዙ ቁጥር አገላለጽ ስህተት መሆኑንና ትክክለኛው ዓለም አቀፍ ስያሜ በአንድ ቁጥር “Strait of Hormuz” (የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ) መባል እንዳለበት ጠቁሟል። በተጨማሪም ቢሊየነሩ ስለ ፋርስ (ፐርሺያ) ስልጣኔ፣ ታሪክ እና ስለ ስፍራው ጥንታዊ አመጣጥ ይበልጥ በጥንቃቄ እንዲያጠና መክሯል።
ይህ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተቀሰቀሰው የቃላት ምልልስ በአሁኑ ወቅት በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ አካባቢ ካለው ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረት እና ከቀጣናው ጂኦፖለቲካዊ ሁኔታ ጋር ተዳምሮ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘንድ ትልቅ የዜና አጀንዳ ሆኖ ቀርቧል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ኢትዮጵያ ከጦር መሳሪያ ግዢ ለመላቀቅ የምታደርገዉ ጥረት በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ላይ አቅሟን ለማጎልበት የሚያግዛት ነዉ ተባለ
ኢትዮጵያ ተተኳሽ ጥይቶችንና ወታደራዊ ድሮኖችን በራሷ ማምረት በመጀመሯ በአገሪቱ የኢኮኖሚና የፀጥታ ሁኔታ ላይ አዲስ ምዕራፍ መከፈቱን የቀድሞ ዲፕሎማት እና የቀድሞ... read more
ከዛሬ ታህሳስ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ (የፋይዳ ቁጥር) ይዞ መቅረብ ግዴታ መሆኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገልጿል፡፡
ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን
መናኸሪያ ሬዲዮ 99.1
ሃሳብ፣አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት የሚከተሉትን የስቱዲዮ ስልኮቻችን ይጠቀሙ
👉011-639-28-52👉011-639-37-63
የቀጥታ ስርጭት 👉 📻 (https://worldradiomap.com/et/play/menaharia) radio 99.1 (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
✅ https://t.me/menaharia_fm
✅https://x.com/MenahriaFm99_1
ትክክለኛውን የመናኸሪያ... read more
በኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን መካከል ለሚገነባው የመንገድ ፕሮጀክት የሚሳተፉ ስራ ተቋራጮችን የተመለከተ መስፈርት መዘጋጀቱ ተገለጸ
ኅዳር 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በቅርቡ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የ738 ነጥብ 2 ሚሊየን ዶላር ብድር መፍቀዷ እና በገንዘቡም በሁለቱ ሃገራት... read more
በኳታር በሚገኘው የአሜሪካ የአየር ማዕከል ቁልፍ የኮሙዩኒኬሽን ጉልላት በኢራን ሚሳኤል ጥቃት ወደመ
ሐምሌ 05 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት እየጨመረ ባለበት ወቅት፣ በኳታር አል ዑዴይድ በሚገኘው የአሜሪካ አየር ማዕከል ላይ ኢራን ባደረሰችው... read more
15ኛው አለም አቀፍ የምልክት ቋንቋ የጥናት እና ምርምር ጉባኤ እየተካሄደ ነው
ጥር 06 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ 15ኛውን አለም አቀፍ... read more
በማርበርግ በሽታ ከተያዙ 11 ሰዎች ውስጥ 6ቱ በበሽታው ህይወታቸው ማለፉ ተገለጸ
ሕዳር 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ከህዳር 5/ 2018 ዓ.ም ጀምሮ የማርበርግ ህክምና ምርመራ ሲደረግ የቆየ ሲሆን በበሽታው ከተጠቁ 11 ሰዎች... read more
“ደህንነቱ የተጠበቀ የጤና ክብካቤ ለሁሉም ጨቅላ ህፃናት እና ህፃናት” በሚል መሪ ቃል የዓለም የታካሚዎች ደህንነት ቀን በላንድማርክ ሆስፒታል ተከበረ
መስከረም 19 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) የዓለም የታካሚዎች ደህንነት ቀን በላንድማርክ ጠቅላላ ሆስፒታል እየተከበረ ነው።
"ደህንነቱን የጠበቀ የጤና ክብካቤ ለሁሉም ጨቅላ... read more
የአባይ ግድብ ምረቃ እና ዓለም አቀፍ ዘገባዎች
ሰኔ 27 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ኢትዮጵያ በመጪው የመስከረም ወር የአባይ ወንዝ ታላቁን ህዳሴ ግድብ (GERD) ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ ስትሆን፣ ይህ ሜጋ... read more
ደረጃ የወጣላቸው ምርቶች ብሔራዊ የደረጃ ምልክት መጠቀም እንዳለባቸው ተገለጸ
አስገዳጅ ደረጃ የወጣላቸው ሁሉም ምርቶች ብሔራዊ የደረጃ ምልክት መጠቀም እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
የኢንስቲትዩቱ የሕዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ ብሩክ ሀብቴ... read more
ምላሽ ይስጡ