ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸው የባህር ኃይል ክፍሏን በታክቲካል የኒውክሌር መሳሪዎች ለማስታጠቅ እና ይበልጥ ግዙፍ የሆኑ ዘመናዊ የጦር መርከቦችን ለመገንባት በከፍተኛ ፍጥነት እየሰራች መሆኑን በይፋ ተናገሩ። መሪው ይህንን ያሉት ሀገሪቱ ባለፈው ዓመት የገነባቻቸው እና በሬክተር ስኬል 5 ሺህ ቶን የሚመዝኑት ሁለት ግዙፍ አጥፊ የጦር መርከቦች መካከል አንደኛዋ የሆነችው “ቾይ ሂዮን” (Choe Hyon) በይፋ ስራ በምትጀምርበት የሹመት ስነ-ስርዓት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው።
ኪም ጆንግ ኡን በናምፖ የወደብ ከተማ በተካሄደው በዚህ ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ የባህር ኃይሉን በኒውክሌር የመሳሪያ ስርዓቶች የማደራጀቱ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ያለምንም መስተጓጎል በተያዘለት መስመር እየተጓዘ ይገኛል። ይህ እርምጃ የሰሜን ኮሪያን የኒውክሌር ኃይል ለማንኛውም ዓይነት ሁለገብ እና ፈጣን ወታደራዊ እርምጃ ዝግጁ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን መሪው በኩራት ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሀገሪቱ በየዓመቱ ሁለት ግዙፍ የጦር መርከቦችን የምትገነባ ሲሆን፥ ወደፊትም እስከ 10 ሺህ ቶን የሚመዝኑ እጅግ ግዙፍ ስልታዊ የጦር መርከቦችን በቅደም ተከተል ወደ ስራ እንደምታስገባ ይፋ አድርገዋል።
ሰሜን ኮሪያ ቀደም ሲል ባወጣችው መግለጫ አዲሷ “ቾይ ሂዮን” የተባለችው የጦር መርከብ የሀገሪቱን እጅግ “ኃያላን መሳሪዎች” የታጠቀች መሆኑን ያረጋገጠች ሲሆን፥ መርከቧ የኒውክሌር ዶንጓዴዎችን እና የክሩዝ ሚሳኤሎችን ጭኖ የመተኮስ ከፍተኛ አቅም እንዳላት ተገልጿል። ይህ በሰሜን ኮሪያ በኩል የታየው አዲስ የባህር ኃይል መዋቅር ሽግግር በአከባቢው በአሜሪካ እና በደቡብ ኮሪያ የሚደረጉ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የታለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የኪም ጆንግ ኡን አዲስ ወታደራዊ አዋጅ በኮሪያ ባህረ-ሰላጤ ላይ ያለውን የደህንነት እና የፖለቲካ ውጥረት ይበልጥ ወደ ከፋ ደረጃ ያሸጋግረዋል ተብሎ የተፈራ ሲሆን፥ በጉዳዩ ዙሪያ የሚወጡ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እንደደረሱን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ሩሲያ ዋትስአፕን ልታግደው እየሞከረች ነው ተባለ
ነሐሴ 08 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) ዋትስአፕ (WhatsApp) የተሰኘው የመልዕክት መላላኪያ መተግበሪያ ሩሲያ አገልግሎቱን ለማገድ እየሞከረች መሆኑን አስታውቋል። ኩባንያው እንደገለጸው፣... read more
ከአንጋፋዋ የኪነጥበብ ሰው #አለምጽሃይ ወዳጆ ጋር የተደረገ ቆይታ
https://youtu.be/NybH5JhdaNs
read more
በፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከ1ሺህ 5መቶ በላይ የእግር መዞር እክል የገጠማቸዉ ህፃናት መገኘታቸው ተገለፀ
የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከዚህ ቀደም ባልተደረገባቸው 10 ክልሎች የተካሄደ ሲሆን ከተቀመጠው እቅድ በላይ ከ5 ዓመት በታች ያሉ ህፃናት መከተባቸውን የኢትዮጵያ... read more
57ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 57ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ከዓለም... read more
ከሰሞኑን በጸደቀው አዋጅ 1387/2017 መሰረት የሚደረገው ምርመራ ከመደበኛው የወንጀል ምርመራ ሂደት በተለየ ዘዴ መሆኑ ተገለጸ
ሰኔ 13 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የቀድሞውን አዋጅ 780/2005ን ለማሻሻል የወጣው እና ሰኔ 10/2017 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጸደቀው አዋጅ 1387/2017... read more
ከገቢ ግብር፣ ታክስና ቀረጥ ጋር ተያይዞ በ2016 በጀት አመት ወደ 309.8 ሚሊዮን ብር ሳይሰበሰብ መቅረቱ ተገለፀ
ሰኔ 17 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2016 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ህጋዊነት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት በዛሬው እለት ለህዝብ... read more
ማንበብና መጻፍን በ18 ዓመቱ የተማሩት ጄሰን አርዴይ የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ታናሽ ጥቁር ፕሮፌሰር ሆኑ
መስከረም 20 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአንዲት እናት ድጋፍና በራሳቸው ጽናት፣ የልጅነት የዕድገት መዘግየትን ተቋቁመው ትምህርታቸውን የተከታተሉት ጄሰን አርዴይ፣ በዓለማችን እጅግ... read more
ማንቸስተር ዩናይትድ በአዲስ ባለሀብት እጅ ሊወድቅ መድረሱን ቱርኪ አል-ሼክ ፍንጭ ሰጡ
መስከረም 29 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሳዑዲ ዓረቢያ የስፖርት እና የመዝናኛ ባለሥልጣን እንዲሁም ታዋቂው የቦክስ ፕሮሞተር ቱርኪ አል-ሼክ የእንግሊዙን ታላቅ ክለብ ማንቸስተር... read more
ከገንዘብ ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ
እ.ኤ.አ ሜይ 25/2025 ሪፖርተር ጋዜጣ “እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ያለበት የውጭ ዕዳ መጠን ከ575 ዶላር መድረሱ ተነገረ" በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር... read more
በትምህርት ቤቶች ለሚደረገው አማተር የኪነ ጥበብ ሰዎችን የማብቃት ስራ ውስጥ አካል ጉዳተኞች በተለያዩ ዘርፎች እንደሚሳተፉ ቢሮው አስታወቀ
የከተማ አስተዳደሩ የኪነ-ጥበብ ዘርፉን ለማሳደግ በሚደርገው አማተር የጥበብ ሰዎችን የማፍራት ስራ ውስጥ ከከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቤቶች ጋር በቅርበት እንደሚሰራ የአዲስ... read more
ምላሽ ይስጡ