ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፥ የቀድሞዋን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን በምስራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ተፅዕኖን እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን በበላይነት የማጠናከር እና የማስተካከል ትልቅ ኃላፊነት እንደሰጧቸው ተሰማ። ይህ የተሰጣቸው አዲስ ተልዕኮ በቀጠናው እየታዩ ያሉ የጸጥታ እና የዲፕሎማሲ መሻከር አዝማሚያዎችን በታዋቂ እና አንጋፋ ዲፕሎማቶች አማካኝነት ለመፍታት ከተያዘው የድርጅቱ ስትራቴጂ ጋር የተያያዘ መሆኑ ታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውስጥ ምንጮች እንደገለጹት፣ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በቀጠናው ባላቸው የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲ ልምድ፣ በተለይም ቀደም ሲል በጅቡቲ፣ በሴኔጋል እና በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (IGAD) እና በአፍሪካ ህብረት የዩኤን ልዩ መልዕክተኛ ሆነው በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ የሰሩ በመሆናቸው ለዚህ ታላቅ ቀጠናዊ ሚና ተመራጭ አድርጓቸዋል።
ዋና ፀሐፊው አንቶኒዮ ጉተሬዝ ይህንን ውሳኔ ያሳለፉት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ለማርገብ፣ በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር መልሶ ለመገንባት እና የድርጅቱን ቀጠናዊ ተሰሚነት ከፍ ለማድረግ ታስቦ መሆኑ ተጠቁሟል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴም በቅርቡ የስልጣን ዘመናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በተለያዩ አህጉራዊ የግጭት አፈታት እና የሰላም ግንባታ ውይይቶች ላይ በንቃት እየተሳተፉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ይህ ሹመት ዩኤን ለአፍሪካ ቀንድ ቀውስ ዘላቂ መፍትሄ ለመፈለግ በወሰደው ስልታዊ እርምጃ ውስጥ ትልቅ ግምት የተሰጠው ሲሆን፥ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እና የሹመቱን ሙሉ ይዘት እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ባለፉት አራት ወራት ውስጥ 420 ሚሊየን ዶላር የውጪ ምንዛሬ ለባንኮች ተሽጧል ተባለ
ሐምሌ 08 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ብሄራዊ ባንክ ከመጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ጀመሮ በየሁለት ሳምንት ሲያካሂደ የነበረው የውጪ ምንዛሬ ጨረታ... read more
“ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የዛሬዉን ትዉልድ ከታሪክ ተወቃሽነት ያዳነ የጋራ አሻራችን ነዉ”👉 ዶ/ር ሂሩት ካሳ
ታላቁ የኢትየጵያ ህዳሴ ግድብ የዛሬውን ትውልድ ከታሪክ ተወቃሽነት ያዳነ የጋራ አሻራችን ነው ሲሉ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ባህል ኪነጥበብ እና ቱሪዝም... read more
ቻይና ለ50 ዓመታት ቻርጅ የማያስፈልገው የሳንቲም መጠን ያለው የኒውክሌር ባትሪ ፈጠረች
መስከረም 21 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የቻይና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችና የምርምር ተቋማት የኃይል አቅርቦትን ትርጉም የሚቀይር አስደናቂ ግኝት ይፋ አደረጉ። በቤታቮልት (Betavolt)... read more
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ለአማራ ክልል ከ5 ሚሊየን ብር በላይ የሚሆን የምግብ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ
ታኅሳስ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል በተከሰተው ድርቅ የከፋ ችግር ላይ ለሚገኙ ዜጎች ከ5 ሚሊዮን ብር... read more
አፍሪካ ላይ የፍልሚያ ሻምፒዮና ይደረጋል
በርካታ የእግርኳስ ቤተሰቦች የአለማችን ትልቁ የሀገራት የውድድር መድረክ የሆነው የአለም ዋንጫ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአህጉራችን አፍሪካ ላይ እንዲከናወን ፊፋ እድሉን... read more
ምክር ቤቱ የውሃ አካል ዳርቻ አወሳሰን፣ ልማት እና እንክብካቤ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጸደቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ31ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የውሃ አካል ዳርቻ አወሳሰን፣ ልማት እና እንክብካቤ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ በሙሉ ደምጽ አጽድቋል፡፡
የውሃ፣... read more
ከጅቡቲ 94 በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎች ወደሀገራቸው ገቡ
ኅዳር 26 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) በጅቡቲ በችግር ውስጥ የነበሩ 94 ኢትዮጵያውያን ወደሀገራቸው መግባታቸው ተገለጸ።
በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከዓለም አቀፍ ፍልሰተኞች... read more
ስጋት የተጋረጠበት የመምህርነት ዘርፍ
https://youtu.be/_H2vPXjiO3M
read more
“ሶላር ኢምፐልስ 2” የተባለች አውሮፕላን በፀሐይ ኃይል ብቻ ዓለምን በመዞር ክብረ ወሰን ሰበረች
👉በዜሮ ነዳጅ፣ በዜሮ ልቀት 40,000 ኪሎሜትሮችን በአንድ ጊዜ መብረር ያስችላታል ነው የተባለው
ሐምሌ 08 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በአቪዬሽን ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው... read more
በኢፌዴሪ አየር ኃይል ውስጥ የተሰራችው ፀሃይ – 2 የተሰኘች አውሮፕላን የመጀመሪያ የሙከራ በረራዋን በስኬት ማጠናቀቋ ተገለጸ
በኢፌዴሪ አየር ኃይል ውስጥ የተሰራችው ፀሃይ - 2 የስልጠና አውሮፕላን የመጀመሪያ የሙከራ በረራዋን በስኬት ማከናወን መቻሏን አየር ኃይሉ አስታውቋል፡፡
ፀሃይ -2... read more
ምላሽ ይስጡ