ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፥ የቀድሞዋን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን በምስራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ተፅዕኖን እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን በበላይነት የማጠናከር እና የማስተካከል ትልቅ ኃላፊነት እንደሰጧቸው ተሰማ። ይህ የተሰጣቸው አዲስ ተልዕኮ በቀጠናው እየታዩ ያሉ የጸጥታ እና የዲፕሎማሲ መሻከር አዝማሚያዎችን በታዋቂ እና አንጋፋ ዲፕሎማቶች አማካኝነት ለመፍታት ከተያዘው የድርጅቱ ስትራቴጂ ጋር የተያያዘ መሆኑ ታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውስጥ ምንጮች እንደገለጹት፣ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በቀጠናው ባላቸው የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲ ልምድ፣ በተለይም ቀደም ሲል በጅቡቲ፣ በሴኔጋል እና በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (IGAD) እና በአፍሪካ ህብረት የዩኤን ልዩ መልዕክተኛ ሆነው በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ የሰሩ በመሆናቸው ለዚህ ታላቅ ቀጠናዊ ሚና ተመራጭ አድርጓቸዋል።
ዋና ፀሐፊው አንቶኒዮ ጉተሬዝ ይህንን ውሳኔ ያሳለፉት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ለማርገብ፣ በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር መልሶ ለመገንባት እና የድርጅቱን ቀጠናዊ ተሰሚነት ከፍ ለማድረግ ታስቦ መሆኑ ተጠቁሟል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴም በቅርቡ የስልጣን ዘመናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በተለያዩ አህጉራዊ የግጭት አፈታት እና የሰላም ግንባታ ውይይቶች ላይ በንቃት እየተሳተፉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ይህ ሹመት ዩኤን ለአፍሪካ ቀንድ ቀውስ ዘላቂ መፍትሄ ለመፈለግ በወሰደው ስልታዊ እርምጃ ውስጥ ትልቅ ግምት የተሰጠው ሲሆን፥ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እና የሹመቱን ሙሉ ይዘት እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
መንግስት ጋብቻን የሚያበረታቱና ለቤተሰብ መጽናት አጋዥ የሚሆን ፖሊሲ ሊቀርጽ ይገባል ተባለ
ከጊዜ ወደ ጊዜ ከጋብቻዉ ቁጥር በዘለለ የሚሰማ የፍቺ ቁጥር እየተበራከተ በመምጣቱ መንግስት ለጋብቻ እና ቤተሰብ መጽናት የሚሆኑ ፓሊሲና የተለያዩ ህጎችን... read more
ሊቨርፑል በአንፊልድ ተአምር ለመስራት ከፒኤስጂ ጋር ይጋጠማል
ሚያዚያ 06 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሊቨርፑል እና የፓሪስ ሴንት ዠርሜን (PSG) የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሩብ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ዛሬ ምሽት በአንፊልድ... read more
የአለም የመጀመሪያው ሚዛኑን በራሱ የሚጠብቅ የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል በብዛት መመረት መጀመሩ ተገለጸ
መጋቢት 12 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በማምረት የሚታወቀው ኦሞዌይ (OMOWAY) ኩባንያ ኦሞ ኤክስ (OMO X) የተሰኘውንና ሚዛኑን በራሱ መጠበቅ... read more
ባለፉት ሰባት ወራት ከሸቀጦች የወጪ ንግድ ከ3.84 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጣናዊ ትሰስር ሚኒስቴር አስታወቀ
ባለፉት ሰባት ወራት ከሸቀጦች የወጪ ንግድ ከ3.84 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ወይም የእቅዱን 146% አፈፃፀም ውጤት መገኘቱን ዶክተር ካሣሁን... read more
የትራምፕ አስተዳደር በ36 ተጨማሪ ሀገራት ላይ የጉዞ እገዳ ለመጣል ማቀዱ ተገልጿል
የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ማስታወሻ አዲሱ የጉዞ እገዳ እቅድ አፍሪካ፣ ካሪቢያን፣ መካከለኛው እስያ እና የፓሲፊክ አገራትን ያነጣጠረ መሆኑ ተገልጿል።
በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ... read more
በጃፓን ፖለቲካ ውስጥ ውጥረት፤ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ዩይቺሮ ታማኪን ጠቅላይ ሚኒስትርነት እጩ ለማድረግ እየመከሩ ነው
ጥቅምት 04 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በጃፓን የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ያልተጠበቀ ለውጥ እያሳየ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ዋና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ገዥውን የሊበራል ዴሞክራቲክ... read more
በዓሉ ያለአደጋ ክስተት በሰላም እንዲጠናቀቅ የሚከተሉትን ጥንቃቄዎችን እንዲደረግ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል
👉 የበዓል ስራዎቸን በሚከናወኑበት ጊዜ ሁሉንም ስራዎች በተመሳሳይ ጊዜ ከማከናወን መቆጠብና ስራዎችን በቅድመ ተከተል እንዲሁም እንደቤተሰብ አባል ብዛትና ችሎታ ስራን... read more
በትግራይ እንዴት ሰላም ይስፈን? 👉
https://youtu.be/C9t7w_FLFSI
read more
ጃፓን የመሬት ውስጥ አውቶማቲክ የብስክሌት ማቆሚያ ስርዓት ዘረጋች
ነሐሴ 15 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በዓለማችን እጅግ የላቁ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የምትታወቀው ጃፓን፣ የከተማዋን ውበት እና ቅልጥፍና ለማስጠበቅ የሚያስችል አውቶማቲክ የብስክሌት... read more
ባንኮች እስከ ምሽት 3፡30 ሰዓት ድረስ ክፍት እንዲሆኑ የሚያስገድደዉ ደንብ ከባንኮች አሰራር ጋር የማይጣጣም ነዉ ሲል የባንኮች ማህበር አስታወቀ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣው ባንኮች እስከ ምሽት 3:30 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው መመሪያ ከባንኮች አሠራር ጋር የማይጣጣም መሆኑን... read more
ምላሽ ይስጡ