ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸው የባህር ኃይል ክፍሏን በታክቲካል የኒውክሌር መሳሪዎች ለማስታጠቅ እና ይበልጥ ግዙፍ የሆኑ ዘመናዊ የጦር መርከቦችን ለመገንባት በከፍተኛ ፍጥነት እየሰራች መሆኑን በይፋ ተናገሩ። መሪው ይህንን ያሉት ሀገሪቱ ባለፈው ዓመት የገነባቻቸው እና በሬክተር ስኬል 5 ሺህ ቶን የሚመዝኑት ሁለት ግዙፍ አጥፊ የጦር መርከቦች መካከል አንደኛዋ የሆነችው “ቾይ ሂዮን” (Choe Hyon) በይፋ ስራ በምትጀምርበት የሹመት ስነ-ስርዓት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው።
ኪም ጆንግ ኡን በናምፖ የወደብ ከተማ በተካሄደው በዚህ ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ የባህር ኃይሉን በኒውክሌር የመሳሪያ ስርዓቶች የማደራጀቱ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ያለምንም መስተጓጎል በተያዘለት መስመር እየተጓዘ ይገኛል። ይህ እርምጃ የሰሜን ኮሪያን የኒውክሌር ኃይል ለማንኛውም ዓይነት ሁለገብ እና ፈጣን ወታደራዊ እርምጃ ዝግጁ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን መሪው በኩራት ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሀገሪቱ በየዓመቱ ሁለት ግዙፍ የጦር መርከቦችን የምትገነባ ሲሆን፥ ወደፊትም እስከ 10 ሺህ ቶን የሚመዝኑ እጅግ ግዙፍ ስልታዊ የጦር መርከቦችን በቅደም ተከተል ወደ ስራ እንደምታስገባ ይፋ አድርገዋል።
ሰሜን ኮሪያ ቀደም ሲል ባወጣችው መግለጫ አዲሷ “ቾይ ሂዮን” የተባለችው የጦር መርከብ የሀገሪቱን እጅግ “ኃያላን መሳሪዎች” የታጠቀች መሆኑን ያረጋገጠች ሲሆን፥ መርከቧ የኒውክሌር ዶንጓዴዎችን እና የክሩዝ ሚሳኤሎችን ጭኖ የመተኮስ ከፍተኛ አቅም እንዳላት ተገልጿል። ይህ በሰሜን ኮሪያ በኩል የታየው አዲስ የባህር ኃይል መዋቅር ሽግግር በአከባቢው በአሜሪካ እና በደቡብ ኮሪያ የሚደረጉ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የታለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የኪም ጆንግ ኡን አዲስ ወታደራዊ አዋጅ በኮሪያ ባህረ-ሰላጤ ላይ ያለውን የደህንነት እና የፖለቲካ ውጥረት ይበልጥ ወደ ከፋ ደረጃ ያሸጋግረዋል ተብሎ የተፈራ ሲሆን፥ በጉዳዩ ዙሪያ የሚወጡ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እንደደረሱን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ፓርቲው ከተሰረዘ በኋላ የሚያደረጋቸው የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ኢ-ህገ መንግስታዊ እንደሚሆን ተገለጸ
አንድ ፓርቲ ከምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅናውን ካጣ በኋላ የሚያደርገው ማንኛውም እንቅስቃሴ ኢ-ህገ መንግስታዊ ይሆናል ሲሉ የህግና የፌዴራሊዚም ባለሙያዎች ለመናኸሪያ ሬዲዮ... read more
አፍሪካ ዉስጥ በጎች እና ፍየሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሰውን አስከፊ ቫይረስ (ፔስቴ ዴስ ፔቲትስ ሩሚናንት)(PPR) ለመዋጋት የፓን አፍሪካን ፕሮግራም ተጀመረ
አዲስ አበባ በጥር ወር መጨረሻና በየካቲት ወር መጀመሪያ ላይ የአፍሪካ ህብረት ታላላቅ ግቦች እና የፓን አፍሪካ አጀንዳዎች ጋር የተጣጣሙ ወሳኝ... read more
የአሜሪካ ውሳኔና የጤናው ዘርፍ እጣፋንታ
https://youtu.be/D48fnG0q9Dg
read more
በኢትዮጵያ የቡና ቱሪዝምን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
በቡና መገኛነቷ በአለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቀው ኢትዮጵያ ምርቷን በአለም ገበያ በጥሬው በመላክ በገበያው ተወዳዳሪ መሆኗ ይታወቃል፡፡
ምርቱን እሴትን ጨምሮ ለውጭ ገበያ... read more
ኢትዮጵያ ከፈለችዉ የተባለዉ የአስር ቢሊዮን ብር እዳ ተጨማሪ ማብራሪያን የሚፈልግ ነዉ ተባለ
ጥር 22 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት አስር ቢሊዮን ብር እዳ መከፍሏን እንዲሁም በአሁን ወቅት የGDP እና የእዳ ጥምርታዋ ከአራት... read more
በመዲናዋ መዝናኛ ቦታዎች የሚሰሩ ሰራተኞች ቅሬታ
https://youtu.be/en9ekzIubDw
read more
በ80 ዓመት አዛውንት እናት ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ በ80 ዓመት አዛውንት ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በ10 ዓመት ፅኑ... read more
እንቅልፍ ማጣት ጤናማ የአእምሮ ክፍልን ሊያጠፋ እና እርጅናን ሊያፋጥን ይችላል ተባለ
መስከረም 30 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) አዲስ የወጣ የምርምር ውጤት እንደሚያመለክተው በቂ እንቅልፍ አለማግኘት ለአእምሮ ጤና እጅግ አሳሳቢ መዘዝ ያስከትላል። ጥናቱ... read more
ትራምፕ ቲክቶክ አሜሪካ ውስጥ የተወሰነ ጊዜ ሳይዘጋ እንዲቆይ ማድረግ አስፈላጊ ሊሆን እንደሚችል ገለጹ
ታኅሳስ 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የምርጫ ቅስቀሳ በሚያካሂዱበት ወቅት በቲክቶክ በቢሊዮን የሚቆጠር እይታ ማግኘታቸውን የገለጹት ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ... read more
ኢንተርኔት በብርሃን ፍጥነት፣ ጃፓን የዓለም ሪከርድን ሰበረች!
መስከረም 07 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)የጃፓን ተመራማሪዎች ኢንተርኔት በብርሃን ፍጥነት ማስተላለፍ የሚያስችል አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን አስመዝግበዋል። ተመራማሪዎቹ በሴኮንድ 402... read more
ምላሽ ይስጡ