ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሀገራቸው የባህር ኃይል ክፍሏን በታክቲካል የኒውክሌር መሳሪዎች ለማስታጠቅ እና ይበልጥ ግዙፍ የሆኑ ዘመናዊ የጦር መርከቦችን ለመገንባት በከፍተኛ ፍጥነት እየሰራች መሆኑን በይፋ ተናገሩ። መሪው ይህንን ያሉት ሀገሪቱ ባለፈው ዓመት የገነባቻቸው እና በሬክተር ስኬል 5 ሺህ ቶን የሚመዝኑት ሁለት ግዙፍ አጥፊ የጦር መርከቦች መካከል አንደኛዋ የሆነችው “ቾይ ሂዮን” (Choe Hyon) በይፋ ስራ በምትጀምርበት የሹመት ስነ-ስርዓት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው።
ኪም ጆንግ ኡን በናምፖ የወደብ ከተማ በተካሄደው በዚህ ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ የባህር ኃይሉን በኒውክሌር የመሳሪያ ስርዓቶች የማደራጀቱ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ያለምንም መስተጓጎል በተያዘለት መስመር እየተጓዘ ይገኛል። ይህ እርምጃ የሰሜን ኮሪያን የኒውክሌር ኃይል ለማንኛውም ዓይነት ሁለገብ እና ፈጣን ወታደራዊ እርምጃ ዝግጁ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን መሪው በኩራት ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሀገሪቱ በየዓመቱ ሁለት ግዙፍ የጦር መርከቦችን የምትገነባ ሲሆን፥ ወደፊትም እስከ 10 ሺህ ቶን የሚመዝኑ እጅግ ግዙፍ ስልታዊ የጦር መርከቦችን በቅደም ተከተል ወደ ስራ እንደምታስገባ ይፋ አድርገዋል።
ሰሜን ኮሪያ ቀደም ሲል ባወጣችው መግለጫ አዲሷ “ቾይ ሂዮን” የተባለችው የጦር መርከብ የሀገሪቱን እጅግ “ኃያላን መሳሪዎች” የታጠቀች መሆኑን ያረጋገጠች ሲሆን፥ መርከቧ የኒውክሌር ዶንጓዴዎችን እና የክሩዝ ሚሳኤሎችን ጭኖ የመተኮስ ከፍተኛ አቅም እንዳላት ተገልጿል። ይህ በሰሜን ኮሪያ በኩል የታየው አዲስ የባህር ኃይል መዋቅር ሽግግር በአከባቢው በአሜሪካ እና በደቡብ ኮሪያ የሚደረጉ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት የታለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የኪም ጆንግ ኡን አዲስ ወታደራዊ አዋጅ በኮሪያ ባህረ-ሰላጤ ላይ ያለውን የደህንነት እና የፖለቲካ ውጥረት ይበልጥ ወደ ከፋ ደረጃ ያሸጋግረዋል ተብሎ የተፈራ ሲሆን፥ በጉዳዩ ዙሪያ የሚወጡ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እንደደረሱን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ራስ ገዙ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ለምሁራን የሰጠሁት “በህግ የተቀመጠ መብት ስላለኝ ነው” ብሏል
👉ትምህርት ሚኒስቴር በበኩሉ ስለተሰጠዉ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ መረጃ እንደሌለዉ ገልጿል፡፡
ታኅሳስ 17 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ትምህርት ሚኒስቴር ከሰሞኑ የፕሮፌሰርነት ማእረግ መስጠት ጉዳይ... read more
“የቆዳ ባንክ/ልገሳ በኢትዮጵያ መጀመር አለባት”የቃጠሎ ህክምናን ባለሙያዎች
ሰብዓዊ ፍጡር የሆነው የሰው ልጅ በተፈጥሮው በርካታ ድንቅ ስጦታዎች ተሰጥተውታል። ከእነዚህም መካከል ትልቁና የመጀመሪያው የሰውነት አካል የሆነው ቆዳው ነው።
የሰውነት ቆዳ... read more
የአጥንት ጤና ለጭንቅላት ንቃትና ለትውስታ ያለውን ወሳኝ ሚና ተመራማሪዎች ይፋ አደረጉ
ግንቦት 06 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) አጥንቶቻችን የሰውነታችንን ቅርፅ ከመያዝ ባለፈ እንደ ልብ እና ሳንባ ሁሉ ንቁ የሆርሞን አመንጪ አካል መሆናቸው... read more
በክልል ከተሞች በቤቲንግ ውርርድ ዘርፍ የተሰማሩ ግለሰቦችን መቆጣጠር ባለመቻሉ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች ለችግር እየተጋለጡ ነው ተብሏል
ኅዳር 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ባለፉት ጊዜያት በመዲናዋ በቤቲንግ ውርርድ ዘርፍ የተሰማሩ አካላት ህገ-ወጥ ድርጊትን መቆጣጠር ተችሏል ቢባልም፤ አሁንም ድረስ... read more
በኢትዮጵያ በአደባባይ ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ በኦሮሞ ማኅበረሰብ ዘንድ በመስከረም ወር ላይ የሚከበረው የኢሬቻ በዓል ተጠቃሽ ነው።
የኢሬቻ በዓል ከገዳ ሥርዓት ጋር እንደሚገናኝና በኦሮሞ ማኅበረሰብ ዘንድ ለዘመናት ሲከበር እንደቆየ የታሪክ ምሁራን ይናገራሉ። በዓሉ መስከረም ከገባና የመስቀል በዓል... read more
የፈረንጆች አዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ርችት እንደሚተኮስ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ
ታኅሳስ 22 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የደህንነትና ልዩ ኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ዛሬ ታህሳስ 22 ቀን 2017... read more
መናኸሪያ #ሞግዚት
🔰ቅሬታ ያስነሱት የመዲናዋ ማሳጅ ቤቶች
በመዲኗ አሁን አሁን የማሳጅ አገልግሎት እንሰጣለን የሚሉ ማስታወቂያዎች ነዋሪዎች በስፋት በሚኖሩባቸው አከባቢዎች ላይ ሳይቀሩ መመልከት እየተለመደ... read more
ለአዶላ ወዮ ከተማ ስታድየም ማደሻ ገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ-ግብር ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ
ታኅሳስ 25 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን አዶላ ወዮ ከተማ የሚገኘውን ስታድየም ለማሳደስ ገቢ ሊሰባሰብ መሆኑን የአዶላ ወዮ ከተማና... read more
የቴሌ ሲስተም በመጠቀም ከግለሰብ አካውንት 238,000ብር የሰረቀች የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኛ ተያዘች
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የቴሌ ሲስተምን በመጠቀም ከግለሰብ አካውንት ብር የሰረቀች የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኛ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሏን የሶዶ... read more
የሞባይል አፕሊኬሽኖች የሳይበር ወንጀለኞች ሰፊ ኢላማ እየሆኑ ነው ተባለ
የሞባይል መተግበሪያዎች (ሞባይል አፕሊኬሽኖች) የግል መረጃዎችን በስፋት በመያዛቸው የሳይበር ወንጀለኞች ዋነኛ ኢላማ እየሆኑ መምጣታቸውን የዘርፉ ባለሙያዎች አስጠነቀቁ።
በተለይም የአይኦኤስ (iOS) ስልኮች... read more
ምላሽ ይስጡ