ሰኔ 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)አገልግሎቱ 100 የከባድ ጭነት ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በሂደት ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ሀገሪቱ የደረሰችበትን የዕድገት ደረጃ የሚመጥን የከባድ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት ለመዘርጋት የ5 ዓመት ዕቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነም ይታወቃል፡፡
የአገልግሎቱ የማርኬቲንግ መምሪያ ኃላፊና ተወካይ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደምሰው በንቲ፤ በመርከብ፣ በከባድ ተሽከርካሪዎችና በሌሎችም ዘርፎች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ ታቅዶ በዚህ ዓመት ብቻ 100 የከባድ ተሽከርካሪዎችን በመግዛት አጠቃላይ ቁጥሩን ወደ 6 መቶ 52 ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ የወደብ ፍላጎቷን ለማሟላት በርካታ ሥራዎችን እየሠራች ባለችበት በአሁኑ ወቅት፤ ፈጣን፣ ዘመናዊና በተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮች የተሳሰሩ አሰራሮችን መዘርጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ አሁን ላይ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በሚያስችል መልኩ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎችን ለማስገባት በሂደት ላይ መሆናቸውን አቶ ደምሰው ተናግረዋል፡፡
የባህር ትራንስፖርት ዘርፉ በሰው ሀብት ማብቃት፣ በዘመናዊ አሠራርና በመሣሪያ አቅርቦት ረገድ በሚጠበቀው ልክ አይደለም ያሉት ዳይሬክተሩ፤ እነዚህን ክፍተቶች ለማሟላት የ5 ዓመት ዕቅድ ተነድፎ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠትና አሠራሩን ለማቀላጠፍ በርካታ የማሻሻያ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በሃገራችን ካሉ ዜጎች በአብዛኛው ከመደበኛ ትምህርት ውጪ የተገኘ የስራ ልምድ ያላቸው ዜጎች መኖራቸው በባለሙያዎች ይገለጻል።
የስራ ልምድ በበቂ ሁኔታ እያላቸው የትምህርት ደረጃን አላሟሉም ተብለው ከስራ የሚቀነሱ በርካታ ባለሙያዎች መኖራቸውም ይንገራል ። በዚህም ረጅም አመት... read more
በመዲናዋ ፍቃድ እና ህጋዊነት ያላቸው ተንቀሳቃሽ የሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች 9ሺህ ብቻ ናቸው ተባለ
ሐምሌ 02 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን እንዳስታወቀው አሁንም ድረስ ያለ ፈቃድ የሚንቀሳቀሱ የሞተር ሳይክል ተጠቃሚዎች ስለመኖራቸው አስታውቋል፡፡
መናኸሪያ... read more
በትግራይ ከሚካሄደዉ የምክክር ሂደት በፊት ልዩ ዉይይት ከወጣቶች ጋር እንደሚኖር ተጠቆመ
ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል የሚካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የምክክር ሂደት ከመጀመሩ አስቀድሞ ከክልሉ ወጣቶች ጋር ልዩ የውይይት... read more
አሜሪካ እና ዩክሬን በሩሲያ ጦርነት ዙሪያ ‘የተሻሻለ’ የሰላም እቅድ ላይ ተስማሙ
ሕዳር 15 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት በዘላቂነት ለማቆም የሚያስችል... read more
የህብረቱ አባል ሀገራት ልምድ የሚለዋወጡበት ጉባኤ እየተካሄድ መሆኑ ተገለጸ
የካቲት 07 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) 38ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ በነገው እለት የህብረቱ አባል ሀገራትና የክብር እንግዶች በተገኙበት የሚካሄድ ሲሆን ከመሪዎች... read more
የዱር እንስሳትን በህይወት የመነገድ እንቅስቃሴ በመቀዛቀዙ ምክንያት የሚፈለገውን ያህል ገቢ እየተገኘ አለመሆኑ ተገለጸ
በኢትዮጵያ የሚገኙ እና ብርቅዬ ያልሆኑ እንዲሁም የመጥፋት አደጋ ያልተጋረጠባቸውን የዱር እንስሳትን አለም አቀፍ ህግና ደንብን በጠበቀ መልኩ በህይወት ለውጭ ሃገር... read more
ከ’ኒያ ፋውንዴሽን ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ እሌኒ ዳምጠው ጋር የተደረገ ቆይታ
https://youtu.be/mGoRJ_xcaHE
read more
ማዕድ ማጋራት የሰው ተኮር እሳቤያችን ተግባራዊ ማሳያ ነው 👉ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ማዕድ ማጋራት የሰው ተኮር እሳቤያችን ተግባራዊ ማሳያ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው... read more
በክልሉ የተቋቋመው ጊዜያዊ ምክር ቤት ውሳኔ ሰጪ መሆኑ ከዚህ ቀደም ሲነሱ የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል ነዉ ተባለ
በትግራይ ክልል ከሳምንታት በፊት የተቋቋመው ጊዜያዊ አማካሪ ካውንስል መፍረሱን እና እሱን የሚተካ ጊዜያዊ ምክር ቤት መቋቋሙ ተገልጿል፡፡ ከ2 ሳምንታት... read more
በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የሰጠው ውክልና የለም ተባለ
ኅዳር 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) “ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፤ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል” በሚል በተለያዩ የማህበራዊ... read more
ምላሽ ይስጡ