ሰኔ 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)አገልግሎቱ 100 የከባድ ጭነት ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በሂደት ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ሀገሪቱ የደረሰችበትን የዕድገት ደረጃ የሚመጥን የከባድ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት ለመዘርጋት የ5 ዓመት ዕቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነም ይታወቃል፡፡
የአገልግሎቱ የማርኬቲንግ መምሪያ ኃላፊና ተወካይ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደምሰው በንቲ፤ በመርከብ፣ በከባድ ተሽከርካሪዎችና በሌሎችም ዘርፎች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ ታቅዶ በዚህ ዓመት ብቻ 100 የከባድ ተሽከርካሪዎችን በመግዛት አጠቃላይ ቁጥሩን ወደ 6 መቶ 52 ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ የወደብ ፍላጎቷን ለማሟላት በርካታ ሥራዎችን እየሠራች ባለችበት በአሁኑ ወቅት፤ ፈጣን፣ ዘመናዊና በተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮች የተሳሰሩ አሰራሮችን መዘርጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ አሁን ላይ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በሚያስችል መልኩ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎችን ለማስገባት በሂደት ላይ መሆናቸውን አቶ ደምሰው ተናግረዋል፡፡
የባህር ትራንስፖርት ዘርፉ በሰው ሀብት ማብቃት፣ በዘመናዊ አሠራርና በመሣሪያ አቅርቦት ረገድ በሚጠበቀው ልክ አይደለም ያሉት ዳይሬክተሩ፤ እነዚህን ክፍተቶች ለማሟላት የ5 ዓመት ዕቅድ ተነድፎ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠትና አሠራሩን ለማቀላጠፍ በርካታ የማሻሻያ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በሰሜን ዋዚሪስታን በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት 13 የጸጥታ ኃይሎች ሲሞቱ 14 ንፁሃን ቆስለዋል
ሰኔ 21 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በፓኪስታን ሰሜናዊ ምዕራብ በሚገኘው ሰሜን ዋዚሪስታን ክልል ውስጥ በተፈጸመ ከባድ የአጥፍቶ ጠፊ የቦምብ ጥቃት 13... read more
አፍሪካ በተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ሁለት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት እንደሚገባ ተጠየቀ
በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው 38ተኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ አፍሪካ በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት እንደሚገባ ተጠይቋል።
የአፍሪካ ህብረት... read more
የጣሪያ ግድግዳ/ንብረት ግብር ተብሎ የወጣውን መመሪያ ክስ በተመለከተ የፍርድ አፈጻጸም ፋይል ለመክፈት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን እናት ፓርቲ አስታወቀ
የንብረት ግብር ማስተባበሪያ ጊዜያዊ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አጥንቶ ያቀረበው በአዲስ አበባ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ አማካኝነት ሚያዝያ 3ቀን 2015 ዓም በተፃፈ ደብዳቤ... read more
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል ቅዳሜ መጋቢት 27/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተባለ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአማራ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ ከመጪው ቅዳሜ መጋቢት 27/2017 ዓ.ም ጀምሮ በባህርዳር ከተማ ለማካሄድ ዝግጅት... read more
የሚፈጸሙ ፆታዊ ጥቃቶችን ለፍትህ ተቋማት የሚያሳዉቁ የማህበረሰብ ክፍሎች አነስተኛ መሆናቸው አሳሳቢ ነው ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ
ጥር 13 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በኢትዮጵያ የሚፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶች እየተበራከቱ መምጣታቸዉን የሚያመላክቱ መረጃ እና ሪፖርቶች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ሆኖም የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ... read more
የወሎ ተሪሸሪ ኬር ሕክምናና የማስተማሪያ ሆስፒታል 23.7 ሚሊዮን ብር ወደ ባንክ እንዳላስገባ የፌዴራል ዋና ኦዲተር አስታወቀ
ኅዳር 30 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የወሎ ተሪሸሪ ኬር... read more
81 በመቶ የሚሆኑ የንግድ ባንክ ደንበኞች የዲጂታል አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸው ተገለ
ታኅሳስ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ባንኩ ዲጂታል ፋይናንስን ለማስፋፋት ካቀደው እቅድ ቀድሞ ማሳካት መቻሉን አመላክቷል፡፡
የዲጂታል ስርዓቱ መስፋፋት በአገልግሎት አሰጣጥ ሒደት... read more
ኢትዮጵያ ከፈለችዉ የተባለዉ የአስር ቢሊዮን ብር እዳ ተጨማሪ ማብራሪያን የሚፈልግ ነዉ ተባለ
ጥር 22 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት አስር ቢሊዮን ብር እዳ መከፍሏን እንዲሁም በአሁን ወቅት የGDP እና የእዳ ጥምርታዋ ከአራት... read more
የህጻናት ፍትህ የማግኘት መብት ተገቢ ትኩረት እያገኘ አለመሆኑ እንዳሳሰበው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጸ
ህጻናት ለሚገባቸው ፍትህ ተገቢውን ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ረገድ የሚመለከታቸው አካላት በቅጡ እየሰሩ እንዳልሆነ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ለመናኸሪያ ሬዲዮ አስታውቋል።
ዛሬም... read more
በሆሮ ጉዱሩ እና በፊንጫ ስኳር ፋብሪካ የኃይል አቅርቦት መቋረጡ ተገለጸ
የካቲት 18 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ለፊንጫ እና ሻንቡ ሰብስቴሽኖች የኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጠው የጊዶ - ፊንጫ ባለ 230 ኪ.ቮ መስመር በቀን... read more
ምላሽ ይስጡ