ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ማንቸስተር ዩናይትድ የቶተንሃሙን አምበል ክሪስቲያን ሮሜሮን ለማስፈረም የዝውውር ጥያቄ እያዘጋጀ መሆኑ ተዘግቧል።
የ28 ዓመቱ አርጀንቲናዊ ተከላካይ ቶተንሃም በፕሪሚየር ሊጉ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት 17ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁን ተከትሎ፣ በዚህ ክረምት ክለቡን ይለቃል ተብሎ በስፋት ይጠበቃል። አርጀንቲናዊው ጋዜጠኛ ጋስተን ኤዱል እንደዘገበው፤ ማንቸስተር ዩናይትድ ቀጣዩ የተጫዋቹ ማረፊያ ለመሆን ተስፋ በማድረግ ይፋዊ የዝውውር ጥያቄ ለማቅረብ እየተዘጋጀ ይገኛል።
ጊቭሚስፖርት (GiveMeSport) በበኩሉ፣ የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሮሜሮን አሁንም የቡድኑ ወሳኝ አካል አድርጎ ስለሚመለከተው በቀላሉ አሳልፎ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆኑን ገልጿል። የ2022 የዓለም ዋንጫ አሸናፊው ሮሜሮ፣ ክለቡ ቶተንሃም በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ቢሆንም እንኳ ራሱን በፕሪሚየር ሊጉ ካሉ ምርጥ የመሀል ተከላካዮች አንዱ ማድረግ በመቻሉ፣ ቶተንሃሞች ለዝውውሩ ከፍተኛ የገንዘብ መጠን እንደሚጠይቁ ይገመታል።
የትራይባል ፉትቦል (Tribal Football) ዘጋቢው አሌክስ ሮበርትስ በበኩሉ፤ ሮሜሮ በቶተንሃም ያለው የኮንትራት ውል ማፍረሻ 50 ሚሊዮን ዩሮ መሆኑንና ይህንን ገንዘብ ለማቅረብ ዩናይትድ ዝግጁ መሆኑን ገልጾ፤ ተጫዋቹን ከአገሩ ልጅና ከቅርብ ጓደኛው ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ ጋር የማጣመር ዕቅድ እንዳላቸው ዘግቧል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ከጅቡቲ 94 በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎች ወደሀገራቸው ገቡ
ኅዳር 26 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) በጅቡቲ በችግር ውስጥ የነበሩ 94 ኢትዮጵያውያን ወደሀገራቸው መግባታቸው ተገለጸ።
በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከዓለም አቀፍ ፍልሰተኞች... read more
በሶስት ምዕራፍ ለ325 ሺሕ ተዋጊዎች የተሃድሶ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገለጸ
ኅዳር 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በመጀመሪያ ዙር ለ75ሺሕ፤ በሁለተኛው ምዕራፍ 1መቶ ሺሕ፤ በሶስተኛው ዙር ደግሞ 150 ሺሕ ተዋጊዎች ተሃድሶ እንደሚሰጥ... read more
ኮሚሽኑ ለጠቅላላ ጉባኤው የአመካካሪዎች ሥልጠና መስጠት ጀመረ
ሰኔ 11 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በዛሬው ዕለት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪዎች ሁለተኛ ዙር ሥልጠናን በአዲስ አበባ... read more
በሎስ አንጀለስ ሰደድ እሳት ምክንያት የሟቾች ቁጥር ከ24 ማለፉ ተገለጸ
👉እሳቱ ዛሬም ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ እንደቀጠለ ነው ተብሏል፡፡
ጥር 05 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት ሎስ አንጀለስ ከተማ በተከሰተው ሰደድ... read more
ትርክትና ታሪክ ወለድ ችግሮችን ለመፍታት ምሁራን ሃሳብ እንዲያዋጡ ተጠየቀ
በቀሪ የሀገራዊ ምክክር ሂደት የምሁራን ሚና ከፍ ማለት እንዳለበት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዛሬ ባካሄደው ውይይት አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ዛሬ ሰኔ 9... read more
ባለድርሻ አካላት ለተፈናቃዮች ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተገለጸ
የተለያዩ የአዉሮፓ ሀገራት አምባሳደሮች የኢትዮጵያ መንግስት ለስደተኞች እያደረገ ያለዉን ድጋፍ ለመጎብኘት ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውን የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ገልጿል፡፡
በዚህ ወቅትም ባለድርሻ... read more
በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ አስተባባሪነት የተዘጋጀው “ቃል በተግባር፤ ከምርጫ እስከ ምርጫ” የተሰኘ አውደ ርዕይ ተከፍቷል
መጋቢት 24 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኤግዚቢሽን አውደ ርዕይ “ቃል በተግባር፤ ከምርጫ እስከ ምርጫ” በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት... read more
በማይናማር ታግተው የነበሩ 246 ዜጎችን በቀጣይ ሳምንት ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
በማይናማር ታግተው የነበሩ ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል... read more
በፈረንሳይ፣ ቁራዎች ጽዳት ሰራተኛ ሆኑ
መስከረም 08 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በምዕራብ ፈረንሳይ የሚገኘው ታዋቂው የ"ፑይ ዱ ፉ" የመዝናኛ መናፈሻ፣ ልዩ የሆነ የጽዳት መርሃ ግብር በመጀመሩ የመናፈሻው... read more
በህገ ወጥ መንገድ 24 ሰዎችን ሲያጭበረብሩ የተገኙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ተቋም አካባቢ በመሆን አስቸኳይ ፓስፖርት አገልግሎት መሰጠት ቆሟል እኛ እናሰራላችሁ በማለት ተቋሙ ለ5 ቀን 20 ሽህ የሚያስከፍለውን... read more
ምላሽ ይስጡ