ግንቦት 12 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአሜሪካ በተለያዩ ግዛቶች በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፉ የመጡት የሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) መረጃ ማዕከላት በአቅራቢያቸው በሚኖሩ ነዋሪዎች ላይ አስከፊ የአካል እና የስነ-ልቦና ጤና እክል እያስከተሉ መሆኑ ይፋ ሆኗል። ማዕከላቱን በማንቀሳቀስ ላይ ከሚገኙት ግዙፍ ወታደራዊ መሰል ማሽነሪዎች የሚወጣው ድምፅ አልባ ንዝረት ለአካባቢው ማህበረሰብ ታላቅ ስጋት ሆኗል።
በማዕከላቱ አቅራቢያ የሚኖሩ በርካታ ዜጎች በየቀኑ ከፍተኛ የሆነ ራስ ምታት፣ ማዞር፣ የማቅለሽለሽ ስሜት፣ የጆሮ ውስጥ ጩኸት እና ከእቅልፍ እጥረት ጋር የተያያዙ ከባድ የጤና ችግሮች እያጋጠሟቸው መሆኑን በምሬት እየገለጹ ይገኛሉ።
ለዚህ ቀውስ ዋነኛው መንስኤ ከማዕከላቱ የሚወጣው “ኢንፍራሳውንድ” (Infrasound) የተባለው እጅግ ዝቅተኛ ድግግሞሽ ያለው የድምፅ ንዝረት መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፣ ይህ ንዝረት ከተለመደው የሰው ልጅ የመስማት አቅም በታች በመሆኑ በተራ የድምፅ መለኪያ መሣሪያዎች ላይ ሳይመዘገብ ሙሉ በሙሉ ጸጥተኛ መስሎ የሰውን አካል ግን በከፍተኛ ሁኔታ የሚጎዳ ነው ተብሏል።
እነዚህ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ተቋማት ሰርቨሮችን ለማቀዝቀዝ የሚያገለግሉ የኢንዱስትሪ ማራገቢያዎችን፣ ተርባይኖችን እና ግዙፍ የናፍጣ ጄነሬተሮችን በቀን 24 ሰዓት ያለ ምንም ማቋረጥ ያንቀሳቅሳሉ። ይህ ቀጣይነት ያለው ውህድ ንዝረት በአካባቢው ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ የሚገኝ ሲሆን፣ አዳዲስ የሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ ማዕከላት ግንባታ ወደ መኖሪያ መንደሮች እየተጠጋ መምጣቱ ህዝቡን ክፉኛ አስቆጥቷል።
ከአሰቃቂው የድምፅ እና የንዝረት ብክለት በተጨማሪ እነዚህ ማዕከላት የሚበሉት የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን፣ ለቅዝቃዜ የሚጨርሱት በሚሊዮን የሚቆጠር ጋሎን የከርሰ ምድር ውሃ እና የሚያስከትሉት የአየር ብክለት በአሜሪካውያን ዘንድ ተከታታይ የሰላማዊ ሰልፍ እና የቅሬታ ድምፆች እንዲበራከቱ ምክንያት ሆኗል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በአንድ “እምቢታ” የጣሊያንን ሕግ የቀየረችው የ17 ዓመት ወጣት ድፍረት!
👉ክብርን ለመጠበቅ ደፋሪን ማግባት ግዴታ ነው የተባለችው ፍራንካ ቪዮላ ማን ናት?
ጥቅምት 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የዛሬ ዓመታት በፊት በጣልያን ሲሲሊ ክልል... read more
ባለፉት ሰባት ወራት ከሸቀጦች የወጪ ንግድ ከ3.84 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጣናዊ ትሰስር ሚኒስቴር አስታወቀ
ባለፉት ሰባት ወራት ከሸቀጦች የወጪ ንግድ ከ3.84 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ወይም የእቅዱን 146% አፈፃፀም ውጤት መገኘቱን ዶክተር ካሣሁን... read more
በመጪው ሳምንት የደሴ ሙዚየም ለጎብኝዎች ክፍት እንደሚሆን ተገለጸ
በደሴ ሙዜም የተዘረፉ ቅርፆችን ለማሰባሰብና ሙዚየሙ ዘመኑን በዋጀ መልኩ በኢዲስ መልክ ለማደስ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለአደራ ማህበር ከብሪትሽ ካውንስል ባገኘው 25... read more
የውጭ አገር ዜጎች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነትን በምን መልኩ?
👉
https://youtu.be/MiNUlahQOXk
read more
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚገኘው የጉዛራ ቤተ መንግስት የጥገና ስራ አለመጠናቀቁ ተገለጸ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚገኘው የጉዛራ ቤተ መንግስት ጥንታዊ እና ታሪካዊ ከሆኑ እንዲሁም በዓለም ቅርስነት ከተመዘገቡ ቅርሶች መካከል አንዱ ሲሆን ቤተ... read more
ተሳፋሪው አየር ላይ በሩን ለመክፈት የሞከረበት አውሮፕላን በረራውን አቋረጠ
ከጃፓን ዋና ከተማ ቶኪዮ ተነስቶ ወደ አሜሪካዋ ግዛት ቴክሳስ በመጓዝ ላይ ያለ አውሮፕላን ውስጥ አንድ ተሳፋሪ የአውራፕላኑን በር ለመክፈት በመሞከሩ... read more
በስፔን ከ39,000 ሄክታር በላይ መሬት በሰደድ እሳት ተቃጥሏል ተባለ
👉በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መሰደዳቸውም ተመላክቷል
ነሐሴ 05 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ስፔን ውስጥ ከ39,000 ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት በሰደድ እሳት መቃጠሉን የሀገሪቱ... read more
ኢትዮጵያ የጅቡቲን ውሳኔ ዘላቂ ወዳጅነትን ማዕከል በአደረገ መልኩ መመልከት እንደሚገባት ተጠቆመ
በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የጅቡቲ መንግስት በሀገሪቱ የሚኖሩና ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ዜጎች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ማስታወቁን ተከትሎ በተቀመጠው ቀነ ገደብ... read more
ቅዱስ ሲኖዶስ ለትግራይ አህጉረ ስብከት ለሚገኙ አባቶች ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን አስተላለፈ
ጥቅምት 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ይህ የተገለፀው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ መጠናቀቁን ተከትሎ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ... read more
ምላሽ ይስጡ