ሕዳር 02 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በግንቦት ወር 2000 ዓ.ም የ’አይ ላቭ ዩ’ (ILOVEYOU) ቫይረስ በታሪክ እጅግ አውዳሚ ከሆኑ የሳይበር ጥቃቶች አንዱ በመሆን ዓለምን ያናጋ ነበር። ይህ ቫይረስ የተፈጠረው በ23 ዓመቱ ፊሊፒናዊ ተማሪ ኦኔል ዴ ጉዝማን ሲሆን፣ በኢሜል አማካኝነት ‘LOVE-LETTER-FOR-YOU.TXT.vbs’ በሚል የፍቅር ደብዳቤ መስሎ ተሰራጨ።
ተንኮል የተሞላበት ኢሜይል በመጠቀም ተጠቂዎች “ILOVEYOU” በሚል ርዕስ የመጣውን ኢሜል ከፍተው አባሪ የሆነውን ፋይል (attachment) ሲከፍቱ፣ ቫይረሱ ኮምፒዩተራቸውን ወዲያውኑ ይበክል ነበር። ከተበከለ በኋላ ቫይረሱ በተጠቂው መዝገብ ዝርዝር ውስጥ ላሉት (contact list) ሰዎች በሙሉ ራሱን በራስ ሰር በመላክ በፍጥነት ተሰራጨ።
በዚህ የሳይበር ጥቃት በአጭር ጊዜ ውስጥ ከአሥር ሚሊዮን በላይ ኮምፒዩተሮች በመበከላቸው በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ የመረጃ እና የስራ መስተጓጎል አስከትሏል። በጥቃቱ ምክንያት የደረሰው የገንዘብ ኪሳራ ግምት ደግሞ ሃያ ቢሊዮን ዶላር ደርሷል ተብሎ ይገመታል።
መርማሪዎች የቫይረሱን ምንጭ ተከታትለው የዴ ጉዝማን አፓርታማ ማኒላ ውስጥ መሆኑን ደርሰውበታል። ቫይረሱ የተመሰረተው የኢንተርኔት መዳረሻ የይለፍ ቃሎችን ለመስረቅ በሚያስችል መልኩ ዴ ጉዝማን የጻፈውና በኮሌጅ ያልተቀበለለት የመመረቂያ ጽሑፍ ላይ እንደሆነም ተረጋግጧል። ምንም እንኳን ዴ ጉዝማን ቫይረሱን መፍጠሩን ቢያምንም፣ በወቅቱ ፊሊፒንስ ማልዌር መጻፍ ወይም ማሰራጨት ወንጀል የሚያስቀጣ ሕግ ስላልነበራት ክስ ሳይመሰረትበት ቀርቷል።
ይህ የ’አይ ላቭ ዩ’ ቫይረስ ወረርሽኝ ዓለም ለዲጂታል ጥቃቶች ምን ያህል ተጋላጭ እንደነበረ በግልጽ አሳይቷል። ለዚህም ምላሽ ለመስጠት በዓለም ዙሪያ ያሉ በርካታ አገራት የሳይበር ደህንነት ሕጎቻቸውን እንዲያሻሽሉና ትላልቅ ለውጦችን እንዲያደርጉ መሪ ምክንያት ሆኗል።
የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ 👉 https://t.me/menaharia_fm
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን 📞
👉011-639-28-52
👉011-639-37-63 (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
ምላሽ ይስጡ