ነሐሴ 07 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም ዳይሬክተር ዶክተር ብርሃኑ አበራ የሚከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች የራሳቸው የሆነ ሂደት እንዳላቸው ገልጸው፤ እንደ ማሳያም ከቅድመ-ምልክት ጀምሮ በተደጋጋሚ እና በቁጥር በርከት ብለው የመሬት መፈራረስ የሚያስከትሉትን በማንሳት አብራርተዋል።
ተቋሙ የስነ-መሬት እንቅስቃሴዎችን በቋሚነት በመከታተልና በመመዝገብ ላይ እንደሚገኝም ዳይሬክተሩ አክለዋል። ተቋሙ የክትትልና የጥናት ስራዎቹን ውጤታማ ለማድረግ ከተለያዩ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝና ለአብነትም ከኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ፣ ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር አስማምሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የመመዝገብ አቅም ያላቸውና «ብሮድ ባንድ» በመባል የሚታወቁ ዘመናዊ መሣሪያዎችን በመጠቀም ላይ እንደሚገኙ የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ እነዚህ መሣሪያዎች በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚከሰቱና በሬክተር ስኬል ከ4.5 በላይ የሆኑ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶችን በስፋት የመመዝገብ አቅም ያላቸው ናቸው ብለዋል። አብዛኞቹ መሣሪያዎች ውድ በመሆናቸው በዓለም አቀፍ ድጋፍና በጋራ ትብብር የተገኙ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
ሆኖም ግን የኢትዮጵያ የቆዳ ስፋት ሰፊ በመሆኑና የመሬት መንቀጥቀጥ ስጋት ያለበት ሁኔታ በመኖሩ፣ በዘርፉ የሚሰሩ ባለሙያዎችና ተቋማት ቁጥር አሁንም በቂ አለመሆኑን ዶክተር ብርሃኑ ተናግረዋል።
በርካታ ተቋማትና በቂ የስነ-መሬት ባለሙያዎች የሚያስፈልጉ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ያለው የሰው ኃይል እጥረት ለዘርፉ ትልቅ ፈተና ሆኖ መቀጠሉ ተመላክቷል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ በኢትዮጵያ ከሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት እያካሄደ ነው።
ውይይቱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር... read more
ህንድና ካናዳ ከ10 ወራት በኋላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማደስ አዲስ ከፍተኛ መልዕክተኛ ሰየሙ
ነሐሴ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ህንድ እና ካናዳ ለ10 ወራት ያህል ተቋርጦ የቆየውን ከፍተኛ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማደስ የሚያስችላቸውን አዲስ መልዕክተኞች... read more
በተቋማት ዉስጥ ያሉ የጥራት ችግሮችን በትብብር ለመቅረፍ በሚዘጋጁ የጥራት ዉድድሮች ላይ የተሳታፊዎች ፍላጎት ዝቅተኛ ነዉ ተባለ
ጥር 07 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሃገር አቀፍ ደረጃ ለ12ኛ ጊዜ የተዘጋጀው የጥራት ውድድር በይፋ ጥር 5 2017 ዓ.ም በተሳታፊዎች ምዝገባ... read more
ኢትዮጵያ በአፋጣኝ የራሰዋን የንግድ ሰርአት ፖሊሲ በማሻሻል አሜሪካ ካወጣችዉ አለም አቀፍ ፖሊሲ ጋር እንዲጣጣም ማድረግ እንደሚገባት ተጠቆመ
በቅርቡ አሜሪካ ባስተላለፈችው የታሪፍ ማሻሻያ መሰረት ኢትዮጵያ ምን አይነት ስራዎች ይጠበቁባታል የሚለዉን መናኸሪያ ሬዲዮ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎችን አነጋግሯል፡፡
ኢትዮጵያ ላይ የንግድ... read more
በኦሮሚያ ክልል የተጀመረው የሠላም ንግግር በሌሎች አካባቢዎችም ሊስፋፋ ይገባል ተባለ
ኅዳር 27 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በኦሮሚያ ክልል የተጀመሩ የሠላም ንግግሮች በሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎችም ተግባራዊ መሆን እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡ የስነ አመራር መምህር... read more
የቀድሞው የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ካቢላ በሃገር ክህደት እና በጦር ወንጀል ክስ የሞት ፍርድ ተፈረደባቸው
መስከረም 21 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ካቢላ የኤም 23 አማፂ ቡድንን በመደገፍ በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክልል ከፍተኛ ውድመት ያደረሰውን ወንጀል ፈጽመዋል ሲል የሃገሪቱ... read more
በአደገኛ ጦር ተወግታ የ100 አመት እድሜ ያስቆጠረች ዓሣ ነባሪ
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአላስካ አዳኞች በተያዘችው ዓሣ ነባሪ ላይ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የተሰራ የጦር ጫፍ መገኘቱ ሳይንቲስቶችን አስገርሟል።
ይህ... read more
በቼክ ሪፐብሊክ ለተሽከርካሪ ወንበር ተጠቃሚዎች ምቹ መንገዶችን የሚያሳይ ካርታ በይፋ ሥራ ላይ ዋለ
ነሐሴ 12 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) የቼክ ሪፐብሊክ መንግስት የአካል ጉዳተኞችን ተንቀሳቃሽነት እና ነጻነት ለማሻሻል ያለመ አዲስ አሰራር በይፋ ተግባራዊ... read more
ሃምሳ በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ጭነት በባቡር ለማጓጓዝ እየተሰራ ነው- የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር
መጋቢት 13 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በየአመቱ የማጓጓዝ አቅሙን እያሳደገ የመጣው የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አ.ማ ሃምሳ በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ጭነት... read more
የሩሲያ ፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባዔ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
የሩሲያ ፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባዔ ቫለቲና ማትቬንኮ በኢትዮጵያ የነበራቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተገልጿል፡፡
ለአፈ-ጉባዔዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ... read more
ምላሽ ይስጡ