ሐምሌ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአትሌቲኮ ማድሪድ ክለብ የፖርቹጋሉን ስፖርቲንግ ሊዝበን አምበል እና የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን አማካኝ ሞርተን ዩልማንድን ለማስፈረም የተቃረበ ሲሆን፣ በግል ጥቅማጥቅሞች ዙሪያ ከተጫዋቹ ጋር ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሷል።
ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ማትዮ ሞሬቶ እንደዘገበው፤ አትሌቲኮ ማድሪድ ከሊዝበን ጋር የነበረው የ35 ሚሊዮን ዩሮ የመጀመሪያ ጥያቄ ውድቅ ከተደረገበት በኋላ፣ አጠቃላይ የዝውውር ሂሳቡን ወደ 40 ሚሊዮን ዩሮ (35 ሚሊዮን ቋሚ እና 5 ሚሊዮን ዩሮ ተጨማሪ ማበረታቻዎች) በማሳደግ ተጫዋቹን ለማስፈረም ተቃርቧል።
የ26 ዓመቱ አማካኝ እስከ 2031 ዓ.ም የሚያቆየውን የ5 ዓመት ኮንትራት ለመፈረም የተስማማ ሲሆን፣ በአዲሱ ክለቡ የቅድመ-ውድድር ዝግጅት ለመጀመር ወደ ማድሪድ ያመራል ተብሎ ይጠበቃል። አትሌቲኮ ማድሪድ ፊቱን ወደ ዩልማንድ ያዞረው፣ ከዎልቭሱ ጆአኦ ጎሜስ ወኪል ጆርጅ ሜንዴስ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ተከትሎ የዝውውር እቅዱን በመቀየሩ ነው።
ሞርተን ዩልማንድ ባለፈው የ2025/2026 የውድድር ዘመን በፖርቹጋል ፕሪሜራ ሊጋ እና በተለያዩ ውድድሮች ለስፖርቲንግ ሊዝበን በአማካኝ መስመር ላይ ቁልፍ ሚና የነበረው ሲሆን፣ 1 ግብ አስቆጥሮ 1 ለግብ የሚሆን ኳስ ማመቻቸት ችሏል።
አትሌቲኮ ማድሪድ ይህንን ተጫዋች አጥብቆ የፈለገበት ዋነኛው ምክንያት በአሰልጣኝ ዲዬጎ ሲሚዮኒ የጨዋታ ስልት ውስጥ ጠንካራ፣ ኳስ አስጣይ እና መከላከል ላይ ያተኮረ ንቁ የተከላካይ አማካኝ (Defensive Midfielder) እንዲሁም በተከላካይ እና በአጥቂ መስመር መካከል ድልድይ የሚሆን ተጫዋች ስለሚያስፈልገው ነው።
ዩልማንድ በስፖርቲንግ ሊዝበን መሪነቱን እና የአማካኝ ክፍሉን በአግባቡ የመቆጣጠር ብቃቱን ያሳየ በመሆኑ፣ ሲሚዮኒ ለሚገነቡት አዲስ የአማካኝ መስመር ጥንካሬ ዋነኛ ምርጫቸው አድርገውታል፤ ተጫዋቹም በሮጂብላንኮዎቹ ቤት ለ5 ዓመታት የሚያቆየውን ኮንትራት ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ቅዱስ ሲኖዶስ ለትግራይ አህጉረ ስብከት ለሚገኙ አባቶች ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን አስተላለፈ
ጥቅምት 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ይህ የተገለፀው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ መጠናቀቁን ተከትሎ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ... read more
በዝናብ ወቅት የሚከሰት የዶሮ በሽታን ለመከላከል መንግስት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ
ነሐሴ 12 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)የዝናብ ወቅት ለዶሮ በሽታ አምጪ ተህዋስያን መራባትና መስፋፋት አመቺ በመሆኑ፣ መንግስት የባለሙያ ድጋፍና የግንዛቤ ማስጨበጫ... read more
የኦሮሚያ ክልል ሰሞኑን በጅማ ዞን የተከሰተውን ጉዳይ በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል
የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ ውስጥ በኢንቨስትመንት ተሰማርተው ይሰሩ በነበሩት በአቶ ዛኪር አባ ኦሊ ላይ አስደንጋጭ... read more
ባለፉት አስር ቀናት ብቻ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ ለስርቆት መዳረጉ ተገለጸ
ባለፉት አስር ቀናት ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦ.ፒ.ጂ ደብሊው ፋይበር መስመር... read more
በትግራይ ክልል የሜርኩሪ መርዛማ ኬሚካል በከፍተኛ ሁኔታ አደጋ እያደረሰ መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ በማዕድን ዘርፍ ላይ በተደረገ ጥናት በአከባቢው የሜርኩሪ መርዛማ ኬሚካል አጠቃቀም ከፍተኛ አደጋ እያደረሰ መሆኑን ለመናኸሪያ ሬዲዮ የገለጹት በትግራይ ክልል... read more
የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በሀገሪቱ በተለያዩ የከተማ መግቢያና መውጫ ላይ ለኮቴ የሚከፈለው ክፍያ ከተቋሙ እዉቅና ዉጪ ህጋዊ ሽፋን ተሰጥቶት የሚፈጸም ሕገ-ወጥ ተግባር ነዉ አለ
ታኅሳስ 02 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሕዝብና የጭነት አጓጓዞች በሆኑ ተሽከርካሪዎች በየከተማው የሚሰበሰቡ የኮቴ ክፍያዎች ሕጋዊነት የሌላቸዉ መሆኑንና የብዝበዛ ድርጊት እየተፈፀመ... read more
ኢትዮ ቴሌኮም የቀጣይ ሦስት ዓመታት አዲስ ስትራቴጂውን ይፋ አደረገ
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የቀጣይ አድማስ (Next Horizon) በሚል ሃሳብ የሦስት ዓመታት ስትራቴጂ እቅዱን ተቋሙ በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል።
ይህ... read more
ቴሌግራም የተጠቃሚዎችን ደኅንነት በተመለከተ የአቋም ለውጥ አደረገ
ኅዳር 25 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ተጠቃሚያቸው እያደገ ከሚገኙት የማኅበራዊ ሚዲያ የትስስር መተግበሪያዎች መካከል አንዱ የሆነው ቴሌግራም ሲወቀስበት የነበረውን የተጠቃሚዎች ደኅንነት... read more
ሞሀመድ ሳላህ ዘንድሮ ከሻምፒዮንስ ሊጉ ይበልጥ ፕሪሚየር ሊጉን ማሳካት እፈልጋለሁ ሲል ሀሳቡን ሰጥቷል
ታኅሳስ 26 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ግብፃዊው ኮኮብ ፍርኦኑ ሞ ሳላህ ዘንድሮ አይቀመሴ አቋም ላይ ነው የሚገኘው። በወርሀ ታኅሳስ ብቻ በ7... read more
የ2025ቱ የቢግ 5 ኮንስትራክት ኢትዮጵያ ትልቁ የግንባታ ዝግጅት ከሰኔ 19-21 በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ ተገለጸ
ኢትዮጵያ፣ ቅድሚያ በምትሰጠውና ባስቀመጠችው የአሥር ዓመታት እ.ኤ.አ. 2012 – 2022 የምጣኔ ሀብት ዕድገት መሠረት የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ገበያ ዋጋ 67 ቢሊዮን... read more
ምላሽ ይስጡ