ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፥ የቀድሞዋን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን በምስራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ተፅዕኖን እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን በበላይነት የማጠናከር እና የማስተካከል ትልቅ ኃላፊነት እንደሰጧቸው ተሰማ። ይህ የተሰጣቸው አዲስ ተልዕኮ በቀጠናው እየታዩ ያሉ የጸጥታ እና የዲፕሎማሲ መሻከር አዝማሚያዎችን በታዋቂ እና አንጋፋ ዲፕሎማቶች አማካኝነት ለመፍታት ከተያዘው የድርጅቱ ስትራቴጂ ጋር የተያያዘ መሆኑ ታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የውስጥ ምንጮች እንደገለጹት፣ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በቀጠናው ባላቸው የረጅም ጊዜ የዲፕሎማሲ ልምድ፣ በተለይም ቀደም ሲል በጅቡቲ፣ በሴኔጋል እና በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (IGAD) እና በአፍሪካ ህብረት የዩኤን ልዩ መልዕክተኛ ሆነው በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ የሰሩ በመሆናቸው ለዚህ ታላቅ ቀጠናዊ ሚና ተመራጭ አድርጓቸዋል።
ዋና ፀሐፊው አንቶኒዮ ጉተሬዝ ይህንን ውሳኔ ያሳለፉት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ለማርገብ፣ በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር መልሶ ለመገንባት እና የድርጅቱን ቀጠናዊ ተሰሚነት ከፍ ለማድረግ ታስቦ መሆኑ ተጠቁሟል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴም በቅርቡ የስልጣን ዘመናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በተለያዩ አህጉራዊ የግጭት አፈታት እና የሰላም ግንባታ ውይይቶች ላይ በንቃት እየተሳተፉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ይህ ሹመት ዩኤን ለአፍሪካ ቀንድ ቀውስ ዘላቂ መፍትሄ ለመፈለግ በወሰደው ስልታዊ እርምጃ ውስጥ ትልቅ ግምት የተሰጠው ሲሆን፥ አዳዲስ ዝርዝር መረጃዎችን እና የሹመቱን ሙሉ ይዘት እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በሃገራችን ካሉ ዜጎች በአብዛኛው ከመደበኛ ትምህርት ውጪ የተገኘ የስራ ልምድ ያላቸው ዜጎች መኖራቸው በባለሙያዎች ይገለጻል።
የስራ ልምድ በበቂ ሁኔታ እያላቸው የትምህርት ደረጃን አላሟሉም ተብለው ከስራ የሚቀነሱ በርካታ ባለሙያዎች መኖራቸውም ይንገራል ። በዚህም ረጅም አመት... read more
♻️ስርቆት የፈጸሙ ግለሰቦች ተይዘዋል
👉የቃሉ ወረዳ ፓሊስ ጽ/ቤት ከኮምቦልቻ ቁጥር 2 እስከ ኮምቦልቻ ቁጥር 1 በተዘረጋ 132 ኪሎ ቮልት ተሸካሚ የኤሌክትሪክ ታወር ላይ ስርቆት... read more
በትግራይ ክልል የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ለመፍታት ጥናት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
ላለፉት ወራት በትግራይ ክልል የተፈጠረው የነዳጅ እጥረት ከፍተኛ የሆነ የኑሮ ውድነትና ተገቢ ያልሆነ መስተጓጎልን ሲፈጥር እንደነበር ይታወሳል፤ ይህንንም ተከትሎ ችግሩን... read more
የዓለም አእምሮ ጤና ቀን እየተከበረ ይገኛል
መስከረም 29 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የዓለም አእምሮ ጤና ቀን በየዓመቱ መስከረም 30 በዓለም አቀፍ ደረጃ "በድንገተኛ አደጋዎችና ሰብአዊ ቀውስ ወቅት የአእምሮ... read more
አሜሪካ ታሪካዊውን የ1 ሳንቲም (ፔኒ) ምርት በይፋ አቆመች
ሕዳር 04 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የዩናይትድ ስቴትስ ሚንት (የሳንቲም ፋብሪካ) ከ230 ዓመታት በላይ ሲያመርተው የቆየውን የ1 ሳንቲም (ፔኒ) ሳንቲም ምርት በይፋ... read more
በክልሉም ሆነ በጎንደር አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የልብ ቀዶ ጥገና አገልግሎት ባለመሰጠቱ በህክምናው ዘርፍ ተግዳሮት እየተፈጠረ ነው ተባለ
ታኅሳስ 18 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህፃናትም ሆነ የአዋቂዎች የልብ ህክምና አገልግሎት የሚሰጡ ባለሙያዎች እና ህክምናው... read more
አፍሪካ ዉስጥ በጎች እና ፍየሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሰውን አስከፊ ቫይረስ (ፔስቴ ዴስ ፔቲትስ ሩሚናንት)(PPR) ለመዋጋት የፓን አፍሪካን ፕሮግራም ተጀመረ
አዲስ አበባ በጥር ወር መጨረሻና በየካቲት ወር መጀመሪያ ላይ የአፍሪካ ህብረት ታላላቅ ግቦች እና የፓን አፍሪካ አጀንዳዎች ጋር የተጣጣሙ ወሳኝ... read more
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተሰሩ ስራዎች ወደሃገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶች በሃገር ውስጥ በመተካት ከ2.8 ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
ጥር 01 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በተለያዩ ዘርፎች ላይ ሙሉ በሙሉ እና በከፊል ከውጪ በሚገቡ ምርቶች በሃገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎች በመሸፈናቸው ከዚህ... read more
ድምፃዊ ዓምደ-ገብርኤል አድማሱ አዲሱን “ወሄነት” የሚል መጠሪያ ያለውን ሶስተኛ አልበሙን የፊታችን እሁድ ለሙዚቃ አፍቃርያን ሊያቀርብ ነው
ሰኔ 19 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ከአሁን በፊት "ሰበበር ኤነዌ" እና "ሟን ያትገፍሬ" በተሰኙት ሁለት የጉራጌኛ አልበሞቹ እንዲሁም በተለየ መልኩ "እያ ኧረሙድን... read more
በወጣቶች ስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል ስምምነት መደረጉ ተገለጸ
የፌደራል የስነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ከኢትዮጵያ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ማህበር ጋር በስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን... read more
ምላሽ ይስጡ