ሰኔ 18 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) 42ኛው የሻምበል አበበ በቂላ ማራቶን የፊታችን እሁድ በሲዳማ ክልል ርዕሰ መዲና ሀዋሳ ከተማ በድምቀት እንደሚካሄድ ተጠቆመ። ከደቂቃዎች በፊት በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጽሕፈት ቤት በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ ተሰጥቷል።
ይህ ታሪካዊ የሩጫ ውድድር በ12 ክለቦች እና በ4 የክልል ቡድኖች በድምሩ በ16 ክለቦች መካከል የሚከናወን ሲሆን፥ በሴት 74 እና በወንድ 249 በአጠቃላይ 323 አትሌቶች የሚሳተፉበት ይሆናል። ከዚህ በተጨማሪም ለአንጋፋ አትሌቶች በተዘጋጀው ልዩ ምድብ ውስጥ እስከ 50 የሚጠጉ ተወዳዳሪዎች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
ውድድሩን በበላይነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የሜዳሊያ እና ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች የገንዘብ ሽልማት የተዘጋጀ ሲሆን፥ በዚህም መሠረት አንደኛ ለሚወጡ 50 ሺህ፣ ሁለተኛ ለሚወጡ 25 ሺህ እንዲሁም ሦስተኛ ደረጃን ይዘው ለሚያጠናቅቁ 20 ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከት ታውቋል። ፌዴሬሽኑ ለአጠቃላይ የገንዘብ ሽልማት ብቻ ከ400 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የመደበ መሆኑም በመግለጫው ላይ ይፋ ሆኗል።
ይህ ውድድር በየዓመቱ የሚከናወን እና ለአገሪቱ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራት ዓይነተኛ ሚና የሚጫወት ትልቅ የውድድር ምዕራፍ መሆኑን የፌዴሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሐሪ ጠቁመዋል። በፌዴሬሽኑ የተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ከሚዲያ አካላት ለተነሱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ከተሰጠበት በኋላ ፍጻሜውን አግኝቷል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ምክር ቤቱ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የሦስት ዓመት የስራ አፈፃፀምን እያዳመጠ ይገኛል
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ባካሄደው 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሦስት ዓመት የስራ... read more
ድሪቤ ወልተጂ የመጀመሪያው የግራንድ ስላም ክብርን ካሸነፉ አትሌቶች መካከል አንዷ መሆኗ ተረጋግጧል
በትራክ ውድድሮች ታሪክ ከፍተኛውን የገንዘብ ሽልማት የሚያስገኘው የግራንድ ስላም ውድድር በጃማይካዋ ኪንግስተን ከተማ እየተከናወነ ይገኛል።
በቅርብ አመታት በውድድር ቁጥር ማነስ ምክንያት... read more
የዓለምን ቀልብ የሳበው የሰሜን ኮሪያ የባህር ላይ ወታደራዊ ጉልበት ትርኢት
ሚያዚያ 06 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በባህር ኃይል የጦር መርከብ ላይ በመገኘት፣ አዳዲስ የክሩዝ እና... read more
ግብጽ ኢትዮጵያ ላይ መሠረተ ቢስ ክስ የምትመሰርተው በሰላማዊ መንገድ ዕድገቷን እንዳይፋጠን ለመገደብ መሆኑን ባለሙያዎች ገለጹ
መስከረም 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ግብፅ በየጊዜው አጀንዳ እየቀያየረች ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ የምታሳስተው፣ ኢትዮጵያ እና የተፋሰሱ አገራት በሕዳሴው ግድብ እና... read more
ፕሬዝደንት ትራምፕ የፌዴራል ሪዘርቭ ገዢ የሆኑትን ሊሳ ኩክን ‘በሞርጌጅ ማጭበርበር’ ወንጀል ከስልጣናቸው አነሱ
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የፌዴራል ሪዘርቭ ባንክ ገዢ የሆኑትን ሊሳ ኩክን በሞርጌጅ ማጭበርበር ወንጀል... read more
በ2017 በጀት ዓመት ከውጪ ንግድ ከተገኘው 8 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር፣ 6 ቢሊየን ዶላሩ ከቻይና ጋር በተደረገ የውጭ ንግድ የተገኘ ነው ተባለ
ጥቅምት 11 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ይህ የተገለጸው በኢትዮጵያና በሻንሲ ግዛት የኢኮኖሚ እና ንግድ ልውውጥ ትብብር ኮንፈረንስ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ እና የቻይናን... read more
ፓሪስ ሴንት ጄርሜ ሞሀመድ ሳላህን ለማስፈረም ይፋዊ ንግግር መጀመሩን የፈረንሳዩ ጋዜጣ ሌኪፕ ዘግቧል
ኅዳር 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የ32 አመቱ ግብፃዊው ኮከብ ሞሀመድ ሳላይ የፈረንሳዩን ሀያል ክለብ ለመቀላቀል ይፋዊ በሆነ መልኩ ንግግሮችን መጀመሩ... read more
በአንዳንድ ተቋማት ስር ያሉ አሰሪዎች ለሰራተኞቻቸው ጥብቅና በመቆማቸው ብቻ ከስራ ገበታቸው የመፈናቀል አደጋ እያጋጠማቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ገለጸ
የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን /ኢሰማኮ/ በአንዳንድ ተቋማት ስር የሚገኙ አሰሪዎች ለሰራተኞቻቸው ጥብቅና በመቆማቸው ብቻ ከስራ ገበታቸው የመፈናቀል አደጋ እያጋጠማቸው መሆኑን... read more
የዩ.ኤስ.ኤ.አይ.ዲ. መቋረጥ በኢትዮጵያ ላይ የደቀነው አደጋ
https://youtu.be/2kwjgk-Qmdc
read more
በቀጣይ አስር ቀናት ውስጥ የሚኖረው የአየር ንብረት በአትክልቶችና በሰብሎች እድገት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ አለዉ ተባለ
ታኅሳስ 03 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ፣ በመካከለኛዉና በደቡብ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሌሊትና የማለዳዉ ቅዝቃዜ በአንጻራዊ ሁኔታ የሚጠናከር... read more
ምላሽ ይስጡ