ሰኔ 18 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) 42ኛው የሻምበል አበበ በቂላ ማራቶን የፊታችን እሁድ በሲዳማ ክልል ርዕሰ መዲና ሀዋሳ ከተማ በድምቀት እንደሚካሄድ ተጠቆመ። ከደቂቃዎች በፊት በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጽሕፈት ቤት በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ ተሰጥቷል።
ይህ ታሪካዊ የሩጫ ውድድር በ12 ክለቦች እና በ4 የክልል ቡድኖች በድምሩ በ16 ክለቦች መካከል የሚከናወን ሲሆን፥ በሴት 74 እና በወንድ 249 በአጠቃላይ 323 አትሌቶች የሚሳተፉበት ይሆናል። ከዚህ በተጨማሪም ለአንጋፋ አትሌቶች በተዘጋጀው ልዩ ምድብ ውስጥ እስከ 50 የሚጠጉ ተወዳዳሪዎች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
ውድድሩን በበላይነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የሜዳሊያ እና ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች የገንዘብ ሽልማት የተዘጋጀ ሲሆን፥ በዚህም መሠረት አንደኛ ለሚወጡ 50 ሺህ፣ ሁለተኛ ለሚወጡ 25 ሺህ እንዲሁም ሦስተኛ ደረጃን ይዘው ለሚያጠናቅቁ 20 ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከት ታውቋል። ፌዴሬሽኑ ለአጠቃላይ የገንዘብ ሽልማት ብቻ ከ400 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የመደበ መሆኑም በመግለጫው ላይ ይፋ ሆኗል።
ይህ ውድድር በየዓመቱ የሚከናወን እና ለአገሪቱ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራት ዓይነተኛ ሚና የሚጫወት ትልቅ የውድድር ምዕራፍ መሆኑን የፌዴሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሐሪ ጠቁመዋል። በፌዴሬሽኑ የተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ከሚዲያ አካላት ለተነሱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ከተሰጠበት በኋላ ፍጻሜውን አግኝቷል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ሬናቶ ቭይጋ ወደ ቪላሪያል በቋሚነት ማቅናቱ ተረጋግጧል
ነሐሴ 15 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የስፔኑ ተወካይ ቡድን የክለባቸው ሪከርድ በሆነ ዋጋ ወይም 29.5 ሚሊዮን ዩሮ ለቼልሲ ወጪ የሚያደርጉ ይሆናል።
ይህ... read more
‘’ዛሬ ብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሊዮ አስራ አራተኛ በቫቲካን ተቀብለውናል። ውይይታችን በሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን ለዓለም ሰላም ያለንን የጋራ አቋምም ተወያይተናል። የትምህርት ተደራሽነትን የማስፋት አስፈላጊነትን በተመለከተም የጋራ ስምምነት ይዘናል።’’
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ(ዶ/ር)__
read more
♻️ስርቆት የፈጸሙ ግለሰቦች ተይዘዋል
👉የቃሉ ወረዳ ፓሊስ ጽ/ቤት ከኮምቦልቻ ቁጥር 2 እስከ ኮምቦልቻ ቁጥር 1 በተዘረጋ 132 ኪሎ ቮልት ተሸካሚ የኤሌክትሪክ ታወር ላይ ስርቆት... read more
በሃይማኖት ስም በማህበራዊ ሚዲያ ምን እየተሰራ ነው?
https://youtu.be/T9Bwg-uIffs
read more
አስከሬኖችን አቀዝቅዞ በማቆየት ቴክኖሎጂው ነፍስ ይዘራባቸዋል ብሎ እየሰራ ያለው ኩባንያ መነጋገሪያ ሆኗል
👉አንድ የጀርመን ስራ ፈጣሪ ኩባንያ ለወደፊት ትንሳኤ ሲል የሰዎችን አስክሬን በማቀዝቀዝ ላይ ይገኛል ተብሏል
ነሐሴ 12 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) በበርሊን... read more
በኢትዮጵያ ቋሚ የህፃናት የኩላሊት ዲያሊሲስ ህክምና መስጫ ተቋም አለመኖሩ ተገለጸ
በሃገሪቱ በኩላሊት በሽታ የተጠቁ ህፃናት ዲያሊስስ የሚያደርጉበት የህክምና መስጫ ተቋም አለመኖሩን በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህፃናት ህክምና የኩላሊት ስፔሻሊስ ዶክተር... read more
ስፔን ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ የኃይል ፍጆታዋን ከታዳሽ ኃይል ማግኘቷ ተዘገበ
ሐምሌ 01 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ስፔን በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታዋን ከታዳሽ ኃይል ምንጮች በማግኘት ታሪካዊ ምዕራፍ አስመዘገበች።
ይህ... read more
የተካረረው የትግራይ ፖለቲካ ወዴት ያመራል?
https://youtu.be/zhqDRcOrTJM
read more
ሃምሳ በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ጭነት በባቡር ለማጓጓዝ እየተሰራ ነው- የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር
መጋቢት 13 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በየአመቱ የማጓጓዝ አቅሙን እያሳደገ የመጣው የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አ.ማ ሃምሳ በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ጭነት... read more
ደረጃ የወጣላቸው ምርቶች ብሔራዊ የደረጃ ምልክት መጠቀም እንዳለባቸው ተገለጸ
አስገዳጅ ደረጃ የወጣላቸው ሁሉም ምርቶች ብሔራዊ የደረጃ ምልክት መጠቀም እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
የኢንስቲትዩቱ የሕዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ ብሩክ ሀብቴ... read more
ምላሽ ይስጡ