ሰኔ 13 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የቶዮታው ሊቀመንበር አኪዮ ቶዮዳ (Akio Toyoda) በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው ውስጥ አነጋጋሪነታቸውን ቀጥለዋል። ሁሉም ሰው ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) ብቻ ፊቱን እያዞረ መምጣቱ ትልቅ ስጋት እንደፈጠረባቸው የገለጹት ሊቀመንበሩ፣ ባህላዊ የነዳጅ ሞተሮችን መደገፋቸውን በመቀጠላቸው “ብቸኝነት” እንደሚሰማቸው በግልጽ ተናግረዋል።
ከታዋቂው Carwow የመኪና መድረክ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ ቶዮዳ ሲናገሩ፦ “ከሶስት ወይም ከአራት ዓመታት በፊት፣ ‘የሞተር ሽታ፣ ድምፅ እና ራሱ ሞተሩ ይማርከኛል’ ብዬ በግልጽ የተናገርኩት እኔ ብቻ ነበርኩ” ብለዋል።
በርካታ የመኪና አምራቾች ሙሉ በሙሉ ትኩረታቸውን ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እያዞሩ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ቶዮታ ግን የተለየ መንገድ በመከተል ላይ ይገኛል። ኩባንያው እንደ ሌሎቹ ወደ አንድ አማራጭ ብቻ ከመሮጥ ይልቅ በሃይብሪድ፣ በሃይድሮጅን ቴክኖሎጂ፣ በባህላዊ የነዳጅ ሞተሮች (Combustion Engines) እንዲሁም በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ በአንድነት ኢንቨስት እያደረገ ይገኛል።
ሊቀመንበሩ አክለውም፣ ባህላዊ ሞተሮች አሁንም በገበያው ውስጥ የራሳቸው ትልቅ ቦታ እንዳላቸውና በሞተር ልማትና ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ የብዙ ሺህ ሰራተኞችን የስራ ዕድል እንደሚታደጉ አስገንዝበዋል።
ይህ አነጋጋሪ አስተያየት የተሰጠው ቶዮታ የሙከራ ደረጃ ላይ ያሉ የሃይድሮጅን መኪኖቹን፣ በተለይም የ GR Yaris ሞዴልን በይፋ ባሳየበት በጃፓኑ የሱፐር ታይኪዩ (Super Taikyu) የጽናት እሽቅድምድም ውድድር ላይ መሆኑ ታውቋል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ለ2/3ኛው የአለም ሙቀት መጨመር ተጠያቂ የሆኑት 10 በመቶ የሚሆኑ አለም ላይ ያሉ ሃብታሞች እንደሆኑ ተመራማሪዎች ገልጸዋል
ሀብታሞች የሚጠቀሙበት እና ኢንቨስት የሚያደርጉበት መንገድ የሙቀት ማዕበል እና የድርቅ አደጋን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር አድርጓል ሲሉ ተመራማሪዎች የአየር ንብረት... read more
በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ጊዳሚ ወረዳ ዜጎች ከጸጥታ ችግር ባለፈ በህክምና ግብዓት አቅርቦት እጥረት ምክንያት የከፋ ቀውስ ውስጥ ናቸው ተባለ
ባለፉት 5 ዓመታት በአገራችን የተለያዩ አከባቢዎች በሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮች ምክንያት የበርካቶች ህይወት ማለፉ፤ ንብረት መውደሙ እና የበዙትም ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን... read more
“የማይበገረው የማር አዳኝ”፤ የንቦችን ጥቃት የሚቋቋመው እንስሳ
ታህሳስ 14 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በዱር እንስሳት ዓለም ውስጥ እጅግ ደፋር እንደሆነ የሚነገርለት ሜርካ (Honey Badger)፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የንቦችን መንጋ... read more
አፍጋኒስታን በልጃገረዶች ላይ የጣለውን የትምህርት እገዳ እንዲያቆም ዩኒሴፍ አሳሰበ
ትምህርት መሠረታዊ መብት ብቻ አይደለም ወደ ጤናማ፣ የተረጋጋ እና የበለጸገ ማህበረሰብ የሚወስድ መንገድ ነው ሲሉ የዩኒሴፍ ዋና ዳይሬክተር ካትሪን ራስል... read more
ለሃገር እድገት እንቅፋት ሆኗል የተባለው የደረሰኝ ጉዳይ… 👉
https://youtu.be/CHYhpXmkmYs
read more
ኢትዮጵያ አዲስ የስደተኞች ፖሊሲ እያዘጋጀች ነው ተባለ
ሕዳር 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ኢትዮጵያ የብሄራዊ ጥቅም ማዕከል ያደረገ አዲስ የስደተኞች ፖሊስ ለማውጣት እየሰራች መሆኗን የስደተኞችና ከስደት ተመላሽ አገልግሎት አስታውቋል፡፡
አገልግሎቱ... read more
የሴቶች ተሳትፎ ባልተረጋገጠበት የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እውን ማድረግ እንደማይቻል ተገለጸ
መጋቢት 14 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ከክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጋር በመተባበር በሚያዘጋጀው “ጉሚ በላል” የሃሳብ መድረክ... read more
ኢራን ከአምስት ቀናት በኋላ የተወሰኑ የስልክ ጥሪ አገልግሎቶችን መፍቀድ ጀመረች
ጥር 05 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በኢራን ለሁለት ሳምንታት የቀጠለውን መጠነ ሰፊ ተቃውሞ ተከትሎ መንግስት ጥሎት የነበረውን የኮሙኒኬሽን እገዳ በከፊል ማንሳቱ ተገለጸ።... read more
በኦሮሚያና በአማራ ክልል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
ታኅሳስ 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በኦሮሚያና አማራ ክልል ባሉ ህዝቦች መካከል ዳግም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማስጀመር ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አባ... read more
የምክክር ኮሚሽኑ ከምርጫው በፊት ሀገርን ያግባባ ይሆን?
የፖለቲካ ምህዳርን ማስፋትና ነጻ የሆነ ፖለቲካዊ ከባቢን መፍጠር ለዲሞክራሲና ለልማት ግንባታ አይነተኛ ቁልፍ ሚናን ይጫወታል በሚል ዛሬ ላይ የሰለጠኑ የምንላቸው... read more
ምላሽ ይስጡ