ሰኔ 13 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የቶዮታው ሊቀመንበር አኪዮ ቶዮዳ (Akio Toyoda) በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው ውስጥ አነጋጋሪነታቸውን ቀጥለዋል። ሁሉም ሰው ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) ብቻ ፊቱን እያዞረ መምጣቱ ትልቅ ስጋት እንደፈጠረባቸው የገለጹት ሊቀመንበሩ፣ ባህላዊ የነዳጅ ሞተሮችን መደገፋቸውን በመቀጠላቸው “ብቸኝነት” እንደሚሰማቸው በግልጽ ተናግረዋል።
ከታዋቂው Carwow የመኪና መድረክ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ ቶዮዳ ሲናገሩ፦ “ከሶስት ወይም ከአራት ዓመታት በፊት፣ ‘የሞተር ሽታ፣ ድምፅ እና ራሱ ሞተሩ ይማርከኛል’ ብዬ በግልጽ የተናገርኩት እኔ ብቻ ነበርኩ” ብለዋል።
በርካታ የመኪና አምራቾች ሙሉ በሙሉ ትኩረታቸውን ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እያዞሩ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ቶዮታ ግን የተለየ መንገድ በመከተል ላይ ይገኛል። ኩባንያው እንደ ሌሎቹ ወደ አንድ አማራጭ ብቻ ከመሮጥ ይልቅ በሃይብሪድ፣ በሃይድሮጅን ቴክኖሎጂ፣ በባህላዊ የነዳጅ ሞተሮች (Combustion Engines) እንዲሁም በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ በአንድነት ኢንቨስት እያደረገ ይገኛል።
ሊቀመንበሩ አክለውም፣ ባህላዊ ሞተሮች አሁንም በገበያው ውስጥ የራሳቸው ትልቅ ቦታ እንዳላቸውና በሞተር ልማትና ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ የብዙ ሺህ ሰራተኞችን የስራ ዕድል እንደሚታደጉ አስገንዝበዋል።
ይህ አነጋጋሪ አስተያየት የተሰጠው ቶዮታ የሙከራ ደረጃ ላይ ያሉ የሃይድሮጅን መኪኖቹን፣ በተለይም የ GR Yaris ሞዴልን በይፋ ባሳየበት በጃፓኑ የሱፐር ታይኪዩ (Super Taikyu) የጽናት እሽቅድምድም ውድድር ላይ መሆኑ ታውቋል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የበርገር ኪንግ ሰራተኛ ለ27 አመታት ባለመቅረቱ ከ400 ሺህ ዶላር በላይ የገንዘብ እርዳታ ተሰጠው
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ላስ ቬጋስ ውስጥ በርገር ኪንግ ውስጥ ለ27 አመታት አንድም ቀን ሳይቀር የሰራ አንድ ሰራተኛ በሰራው ታማኝነት... read more
በሎስ አንጀለስ ሰደድ እሳት ምክንያት የሟቾች ቁጥር ከ24 ማለፉ ተገለጸ
👉እሳቱ ዛሬም ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ እንደቀጠለ ነው ተብሏል፡፡
ጥር 05 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት ሎስ አንጀለስ ከተማ በተከሰተው ሰደድ... read more
የአምሰት አመት #የብልፅግና ጉዞ
🔔ከሰብአዊ መብት እስከ ዲሞክራሲ
🔔ከሙስና እሰከ መልካም አስተዳደር
🔔ከውጪ ጉዳይ አስከ ብሔራዊ ጥቅም
🔔ከአመራር እስከ ተቋም ግንባታ
♻️የአምሰት አመት #የብልፅግና ጉዞ ሁሉም ለውይይት ቀርቧል፡፡
ኅዳር... read more
በቀድሞው የጋምቢያ ፕሬዝዳንት ንብረቶች ሽያጭ ላይ ተሰርቷል የተባለው ሙስና የሕዝብ ተቃውሞ አስነስቷል
በአውሮፓውያኑ 1994 በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከያዙ በኋላ ሀገሪቱን ለ22 ዓመታት የመሩት ያሕያ ጃሜህ በ2017 በምርጫ ሲሸነፉ ሀገሪቱን ለቀው ወደ ኢኳቶሪያል... read more
አፍሪካ በተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ሁለት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት እንደሚገባ ተጠየቀ
በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው 38ተኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ አፍሪካ በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት እንደሚገባ ተጠይቋል።
የአፍሪካ ህብረት... read more
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ ገዝነት ለመሸጋገር እየተዘጋጀሁ ነው አለ
ኅዳር 19 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማርና ሌሎች ተግባራትን በላቀ ደረጃ ለመፈፀምና ተወዳዳሪነቱን ለማስቀጠል ወደ ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ... read more
ለ2017/18 የምርት ዘመን ግብዓት 55,000ሜ/ቶን ዳፕ የተሰኘ የአፈር ማዳበሪያ የጫነችው MV DIONISIS የተባለችው 20ኛዋ መርከብ ጅቡቲ ወደብ ደርሳ የማራገፍ ኦፕሬሽን መጀመሯ ተገለጸ
ለ2017/18 የምርት ዘመን ግብዓት የሚሆን 2.4 ሚለዮን ሜትሪክ ቶን ወይም 24,000,000( ሃያ-አራት ሚሊዮን) ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ገዝቶ ወደ አገር ውስጥ... read more
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በ2017 ዓ.ም ከቅጣት 404 ሚሊዮን ብር ገቢ ማሰባሰቡን አስታወቀ
ነሐሴ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከድርጅቶች፣ ከግለሰቦች እና ከመንግስት ተቋማት የተጣለባቸውን የቅጣት... read more
የኖርዌይ ቴክኖሎጂ በሰባት ሰዓታት ውስጥ በረሃማ አሸዋን ወደ ለም አፈርነት ይቀይራል ተባለ
ነሐሴ 19 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኖርዌይ ኩባንያ በሆነው በዴሰርት ኮንትሮል (Desert Control) የተገኘ አዲስ ቴክኖሎጂ በመጠቀም በረሃማ አሸዋን በሰባት ሰዓታት... read more
የህፃናትን መብት እና ደህንነት ለማስጠበቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
የአዲስ አበባ ሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የአፍሪካ ህፃናት ቀንን ምክንያት በማድረግ ህፃናት ከፍተኛ ትኩረትን የሚሹ እንደመሆናቸው በቢሮ ደረጃ... read more
ምላሽ ይስጡ