ነሐሴ 20 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)የመኪና ባለቤቶች እና አሽከርካሪዎች ለተሽከርካሪዎቻቸው ጎማ ሲገዙ ወይም ሲቀይሩ በጎማው ጎን (Sidewall) ላይ የተጻፉትን ቁጥሮች እና ፊደላት ትርጉም ማወቅ ለደህንነታቸው ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ። እነዚህ ምልክቶች የጎማውን መጠን፣ የመሸከም አቅም፣ የፍጥነት ወሰን እና የተመረተበትን ጊዜ የሚገልጹ መረጃዎች ናቸው።
ለአብነት ያህል P205/55R16 91V የሚለውን የጎማ ላይ ምልክት ብንመለከት የመጀመሪያው ፊደል P ጎማው ለሰው ማጓጓዣ (Passenger Vehicle) የተሰራ መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን LT ከሆነ ደግሞ ለቀላል ጭነት (Light Truck) የሚያገለግል ነው።
ቀጥሎ ያለው 205 የጎማውን ጎን ለጎን ስፋት በሚሊሜትር ይገልጻል፤ ቁጥር 55 ደግሞ የጎማው ቁመት ከስፋቱ ጋር ያለውን ንፅፅር በመቶኛ ያሳያል። R የሚለው ፊደል የውስጥ ሽቦዎቹ በክብ የተቀመጡበት (Radial) መሆኑን የሚያመለክት ሲሆን ቁጥር 16 ደግሞ ጎማው የሚገጠምበት ሪም መጠን በኢንች ነው።
በመቀጠል የሚመጣው ቁጥር 91 ጎማው በነጠላ የመሸከም አቅሙን የሚያሳይ ኮድ ሲሆን ይህም እስከ 615 ኪሎ ግራም መሸከም እንደሚችል ያመለክታል። ከጎኑ ያለው V ፊደል ደግሞ ጎማው በደህና ሁኔታ መጓዝ የሚችለውን ከፍተኛ የፍጥነት ወሰን የሚያሳይ ሲሆን እስከ 240 km/h የሚያስኬድ መሆኑን ያብራራል። H (210 km/h) እና T (190 km/h) ሌሎች አብዛኛውን ጊዜ የሚታዩ የፍጥነት ወሰን ምልክቶች ናቸው።
በጎማው ላይ DOT ከሚለው ጽሁፍ መጨረሻ የሚገኘው ባለ 4 ዲጂት ቁጥር የተመረተበትን ሳምንት እና ዓመት ያሳያል። ለምሳሌ 1223 የሚለው ምልክት ጎማው በ2023 በ12ኛው ሳምንት የተመረተ መሆኑን ያመለክታል። ጎማ ምንም እንኳን ጥቅም ላይ ባይውል ከ5 እስከ 6 ዓመታት በላይ ከቆየ የመለጠጥ አቅሙ ስለሚቀንስ ለአደጋ ሊያጋልጥ እንደሚችል ባለሙያዎች ይመክራሉ።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ኤሎን ማስክ በትራምፕ ሪፐብሊካን “ትልቅ፣ ቆንጆ ሂሳብ” ላይ ትችታቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል
ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የስፔስኤክስ እና ቴስላ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤሎን ማስክ በትራምፕ ሪፐብሊካን አስተዳደር የቀረበውን "ትልቅ፣ ቆንጆ ሂሳብ"("big,... read more
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ፓርቲያቸው ባለፉት አምስት አመታት ከጎረቤት ሀገራት ጋር ከቃላት ባለፈ ግጭት ውስጥ አለመግባቱን ገለጹ
ኅዳር 21 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የብልፅግና ፓርቲ ባለፉት አምስት አመታት ከጎረቤት ሃገራት ጋር ከቃላት መወራወር ባለፈ... read more
ከግብፅና ከሱዳን ከሚነሱ ውዝግቦች በተጨማሪ የሀገር ውስጥ የውሃ ሀብት አስተዳደር የግጭት መንስኤ እንዳይሆን ሊሠራ እንደሚገባ ተገለጸ
ሐምሌ 22 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከሰሞኑ ባዘጋጀው በተፋሰስ ምክር ቤት ረቂቅ ደንብ ዙሪያ በተካሄደው የባለድርሻ አካላት የምክክር... read more
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ለመጀመሪያ ጊዜ 39.5 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ
ነሐሴ 22 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ተቋሙ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 96.5 ቢሊዮን ብር ማትረፉን የሃይሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ... read more
የንግድ ባንክ አዲስ የዲጂታል መተግበሪያ፡ “ሲ.ቢ.ኢ በጄ” በይፋ ቀረበ
ሕዳር 02 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ "ሲ.ቢ.ኢ በጄ" (CBE ByG) የተሰኘ አዲስ የዲጂታል መተግበሪያ አማራጭ በይፋ አስተዋውቋል።
ባንኩ ይፋ ያደረገው... read more
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በ2017 ዓ.ም ከቅጣት 404 ሚሊዮን ብር ገቢ ማሰባሰቡን አስታወቀ
ነሐሴ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከድርጅቶች፣ ከግለሰቦች እና ከመንግስት ተቋማት የተጣለባቸውን የቅጣት... read more
ሰበር ዜና፦ ኢራን በባህሬን፣ ኩዌት እና ኳታር በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ መጠነ-ሰፊ የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃት ሰነዘረች
ሐምሌ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ባለፉት ሶስት ሳምንታት ሰፍኖ የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ፣ አሜሪካ በኢራን ደቡባዊ እና ምስራቃዊ ግዛቶች... read more
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ከ70 ግራም በታች የሆኑ የዳቦ ምርቶችን ሲያቀርቡና ሲሸጡ የተገኙ 53 ዳቦ ቤቶች ላይ እስከ ማሸግ የደረሰ እርምጃ መውሰዱን ገለጸ
ታኅሳስ 18 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የንግድ ኢንስፔክሽን እና ሬጉላቶሪ ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ አሰፋ ለጣቢያችን እንደገለጹት ባለፉት... read more
ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ
ጥር 06 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሹመትን አስመልክቶ የቀረበለትን የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ... read more
የኢትዮጵያን ፓስፖርት ለማውጣት ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር የዋሉ የሌሎች ሃገራት ዜጎች ተገቢውን ቅጣት እያገኙ እንዳልሆነ ተገለጸ
ኅዳር 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎች የኢትዮጵያን ፓስፖርት ለማውጣት ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር የዋሉ የጎረቤት ሀገራት ዜጎች በፍርድ ቤት... read more
ምላሽ ይስጡ