ነሐሴ 20 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)የለንደኑ ክለብ ቼልሲ እና ኖቲንግሃም ፎረስት በ23 ዓመቱ እንግሊዛዊ አጥቂ ሊያም ዴላፕ ዝውውር ዙሪያ ሙሉ ስምምነት ላይ ለመድረስ ተቃርበዋል።
ባለፈው ክረምት ከኢፕስዊች ታውን በ30 ሚሊዮን ፓውንድ ስታምፎርድ ብሪጅን የተቀላቀለው ዴላፕ፣ በቼልሲ ቤት ባሳለፈው የመጀመሪያ የውድድር ዘመን በጉዳት እና በአሰልጣኞች መቀያየር ምክንያት በቂ የመጫወት እድል ሳያገኝ ቀርቷል።
ቼልሲዎች መጀመሪያ ላይ ለተጫዋቹ እስከ 50 ሚሊዮን ፓውንድ ይፈልጉ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ዝውውሩን በ45 ሚሊዮን ፓውንድ አካባቢ ለማጠናቀቅ ፈቃደኛ ሆነዋል። ታይዎ አዎኒዪን በ9 ሚሊዮን ፓውንድ ለኮቨንትሪ ሲቲ የሸጡት ኖቲንግሃም ፎረስቶች፣ በኦሊቨር ግላስነር ስር የፊት መስመራቸውን ለማጠናከር ዴላፕን ዋነኛ ኢላማቸው አድርገውታል።
ኤቨርተኖችም በተጫዋቹ ላይ ፍላጎት ቢኖራቸውም፣ ዴላፕ በፕሪሚየር ሊጉ የመቆየት ፍላጎት ያለው በመሆኑ እና ፎረስትም ድርድሩን በመግፋቱ የሕክምና ምርመራውን አጠናቆ ይፋዊ ውል ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
ጉዳት እንዲሁም የአሰልጣኞች መቀያየር ተጫዋቹ በብሪጅ የነበረውን ቆይታ ከባድ አድርገውታል። በቼልሲ ማልያ በፕሪሚየር ሊጉ 1 ጎል ብቻ ነው ማስቆጠር የቻለው። ባጠቃላይ በቼልሲ ቆይታው ባደረጋቸው 47 ጨዋታዎች 3 ጎሎችን ብቻ ነው ማስቆጠር የቻለው።
በ24 ዓመቱ ላይ የሚገኘው እንግሊዛዊው አጥቂ የኖቲንጋም ፎረስት የሪከርድ ግዢ ሆኖ ወደ ሲቲ ግራውንድ የሚያመራ ሲሆን፣ ወጥነት ባለው መንገድ ኳስ እና መረብን ለማገናኘት የሚችልበት ወሳኝ የዕድሜ ክልል ላይ ስለሚገኝ ዕድሉን በሚገባ በሲቲ ግራውንድ ይጠቀማል ተብሎ ይገመታል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
Fact_checking_tools
አሳሳች ወይም እውነትነታቸው ያልተረጋገጡ ምስሎችን ወይም ቪድዮዎችን ለማጣራት የሚጠቅሙ መሳሪያዎች እና የማረጋገጫ መንገዶች
👉Google Reverse Image Search
ይህ የምረጃ ማጣሪያ በፎቶሾፕ ተመሳስለው... read more
ሱዳን ለ30 ወራት ተዘግቶ የቆየውን የካርቱም አውሮፕላን ማረፊያ ልትከፍት ነው
ጥቅምት 11 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ባለፈው ሚያዚያ 2023 በአገሪቱ የጦር ኃይል እና በፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ መካከል ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ በኋላ... read more
ሳውዲ አረቢያ የእስራኤል በሶሪያ ላይ ያደረገችውን ወረራ አወገዘች
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሳውዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል በሶሪያ ግዛት ውስጥ በቅርቡ ያደረገችውን ወረራ በጽኑ አውግዟል። ሚኒስቴሩ... read more
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የብስክሌት ትራንስፖርትን ለማስፋፋት የአሰራር ደንብ እንዲፀድቅ ጥያቄ ማቅረቡን ገለጸ
ታኅሳስ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የብስክሌት ትራንስፖርት ለማስፋፋት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ... read more
አሜሪካ እና ዩክሬን በሩሲያ ጦርነት ዙሪያ ‘የተሻሻለ’ የሰላም እቅድ ላይ ተስማሙ
ሕዳር 15 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት በዘላቂነት ለማቆም የሚያስችል... read more
በአዲስ አበባ ከተማ የዩኒቨርሲቲ መንደር ሊገነባ መታቀዱ ለትምህርት ዘርፉ መነቃቃትን የሚያመጣ ነው ተባለ
ጣቢያችን ያነጋገራቸው የከተማ ልማት እና የኪነ ህንጻ ባለሙያ አቶ ቤንጀዲድ ሃይለሚካኤል ለአንድ ከተማ ከሚያስፈልጉ መሰረተ ልማቶች ውስጥ አንዱ የትምህርት ተቋም... read more
በሶስት ምዕራፍ ለ325 ሺሕ ተዋጊዎች የተሃድሶ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገለጸ
ኅዳር 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በመጀመሪያ ዙር ለ75ሺሕ፤ በሁለተኛው ምዕራፍ 1መቶ ሺሕ፤ በሶስተኛው ዙር ደግሞ 150 ሺሕ ተዋጊዎች ተሃድሶ እንደሚሰጥ... read more
ከ’ኒያ ፋውንዴሽን ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ እሌኒ ዳምጠው ጋር የተደረገ ቆይታ
https://youtu.be/mGoRJ_xcaHE
read more
ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት በትራፊክ አደጋ ቅነሳ በሰራችሁ ስራ ከዓለም አቀፍ ተቋማት እውቅና ማግኘቷ ተገለጸ
ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት በሰራችሁ ስራ ከዓለም አቀፍ ተቋማት እውቅና ማግኘቷን የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ምንም እንኳን አሁንም የትራፊክ አደጋ... read more
ኢትዮጵያ የተቀቀሉ የሥጋ ምርቶችን ወደ ቻይና መላክ ልትጀምር መሆኑ ተገለጸ
ታኅሳስ 18 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ኢትዮጵያ የተቀቀሉ የሥጋ ምርቶች እና ተረፈ ምርቶችን ለቻይና ገበያ ልታቀርብ መሆኑን የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
የእንስሳት... read more
ምላሽ ይስጡ