ሰኔ 18 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) 42ኛው የሻምበል አበበ በቂላ ማራቶን የፊታችን እሁድ በሲዳማ ክልል ርዕሰ መዲና ሀዋሳ ከተማ በድምቀት እንደሚካሄድ ተጠቆመ። ከደቂቃዎች በፊት በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጽሕፈት ቤት በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ ተሰጥቷል።
ይህ ታሪካዊ የሩጫ ውድድር በ12 ክለቦች እና በ4 የክልል ቡድኖች በድምሩ በ16 ክለቦች መካከል የሚከናወን ሲሆን፥ በሴት 74 እና በወንድ 249 በአጠቃላይ 323 አትሌቶች የሚሳተፉበት ይሆናል። ከዚህ በተጨማሪም ለአንጋፋ አትሌቶች በተዘጋጀው ልዩ ምድብ ውስጥ እስከ 50 የሚጠጉ ተወዳዳሪዎች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
ውድድሩን በበላይነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የሜዳሊያ እና ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች የገንዘብ ሽልማት የተዘጋጀ ሲሆን፥ በዚህም መሠረት አንደኛ ለሚወጡ 50 ሺህ፣ ሁለተኛ ለሚወጡ 25 ሺህ እንዲሁም ሦስተኛ ደረጃን ይዘው ለሚያጠናቅቁ 20 ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከት ታውቋል። ፌዴሬሽኑ ለአጠቃላይ የገንዘብ ሽልማት ብቻ ከ400 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የመደበ መሆኑም በመግለጫው ላይ ይፋ ሆኗል።
ይህ ውድድር በየዓመቱ የሚከናወን እና ለአገሪቱ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራት ዓይነተኛ ሚና የሚጫወት ትልቅ የውድድር ምዕራፍ መሆኑን የፌዴሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሐሪ ጠቁመዋል። በፌዴሬሽኑ የተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ከሚዲያ አካላት ለተነሱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ከተሰጠበት በኋላ ፍጻሜውን አግኝቷል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ለሰብዓዊ ድጋፍ የሚወል ከ100 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በሰብል መሸፈኑን የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ
ኅዳር 25 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በየጊዜዉ በሚከሰቱ ሰዉ ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ምክንያት የተረጂ ዜጎች ቁጥር መጨመሩ ይገለጻል፡፡
በዚህም ምክንያት ከቤት... read more
በመጪዉ የክረምት ወቅት ለጎርፍ አደጋ ስጋት የሚሆን ግድብ አለመኖሩ ተገለጸ
በተለያዩ የሐገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የውሃ ሀይል ማመንጫ ግድቦች መጪውን የክረምት ወቅት ተከትሎ ሞልተው የማስተንፈስ ስራ ከመከናወኑ አስቀድሞ ለማህበረሰቡ የጥንቃቄ መልዕክት... read more
ከካንሰር የተሳሳተ ምርመራ ጀርባ የተገኘው አስደንጋጭ እውነት፦ በሰውየው አእምሮ ውስጥ ምን ተገኘ?
ሐምሌ 02 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በስፔን ሀገር የሚኖር አንድ የ60 ዓመት አዛውንት፣ ከቀን ወደ ቀን እየበረታ የመጣ የራስ ምታት ሕመም... read more
ትላንት በምግብ ማብሰያነት ያገለገለው ዘይት የነገ ተሽከርካሪዎችን ነዳጅ ሊሆን እንደሚችል ያውቁ ኖሯል? ከፊንላንድ የተሰማ አስገራሚ የቴክኖሎጂ ስኬት!
ሰኔ 18 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) በየቀኑ በቤታችንም ሆነ በተለያዩ ምግብ ቤቶች ውስጥ ለምግብ ማብሰያነት ተጠቅመን የምንደፋው ወይም የምናስወግደው የቆሸሸ... read more
ከአድዋ ድል ባሻገር….
https://youtu.be/gJFVVdYp7R4
read more
በሪል እስቴት ዘርፉ ለሚነሱ ክፍተቶች የመገናኛ ብዙሃኑም ተጠያቂ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
ታኅሳስ 02 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሪል እስቴት ዘርፉ ዋጋ መወደድ ዜጎች የቤት ባለቤት የመሆን እድላቸውን እንዳመናመነው ይገለጻል፡፡ በዚህ ሒደት ውስጥ መገናኛ... read more
በጸጥታ ችግር ምክንያት ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ የተቋረጠው የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት እስካሁን መፍትኤ ባለማግኘቱ ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠናል ሲሉ የኮሬ ዞን ነዋሪዎች ገለጹ
በቀደመው ስያሜው የአማሮ ልዩ ወረዳ በሚል የሚታወቀው አከባቢው ከአዲሱ የክልል አደረጃጀት በኃላ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስር ከሚገኙ ዞኖች መካከል አንዱ... read more
የአፍሪካ መሪዎች አዲሱን ዓመት በሰላም እና አንድነት እንዲያሳልፉ ጥሪ ቀረበ
ታኅሳስ 25 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሳህል ቀጠና እና የምስራቅ አፍሪካ መሪዎች ለሰላም እና መረጋጋት አፅንኦት እንዲሰጡ የኬንያው ፕሬዝዳንት ጠይቀዋል፡፡
የአፍሪካ መሪዎች አዲሱን... read more
ማንበብና መጻፍን በ18 ዓመቱ የተማሩት ጄሰን አርዴይ የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ታናሽ ጥቁር ፕሮፌሰር ሆኑ
መስከረም 20 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአንዲት እናት ድጋፍና በራሳቸው ጽናት፣ የልጅነት የዕድገት መዘግየትን ተቋቁመው ትምህርታቸውን የተከታተሉት ጄሰን አርዴይ፣ በዓለማችን እጅግ... read more
ምላሽ ይስጡ