ሰኔ 18 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) 42ኛው የሻምበል አበበ በቂላ ማራቶን የፊታችን እሁድ በሲዳማ ክልል ርዕሰ መዲና ሀዋሳ ከተማ በድምቀት እንደሚካሄድ ተጠቆመ። ከደቂቃዎች በፊት በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጽሕፈት ቤት በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ ተሰጥቷል።
ይህ ታሪካዊ የሩጫ ውድድር በ12 ክለቦች እና በ4 የክልል ቡድኖች በድምሩ በ16 ክለቦች መካከል የሚከናወን ሲሆን፥ በሴት 74 እና በወንድ 249 በአጠቃላይ 323 አትሌቶች የሚሳተፉበት ይሆናል። ከዚህ በተጨማሪም ለአንጋፋ አትሌቶች በተዘጋጀው ልዩ ምድብ ውስጥ እስከ 50 የሚጠጉ ተወዳዳሪዎች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
ውድድሩን በበላይነት ለሚያጠናቅቁ አትሌቶች የሜዳሊያ እና ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች የገንዘብ ሽልማት የተዘጋጀ ሲሆን፥ በዚህም መሠረት አንደኛ ለሚወጡ 50 ሺህ፣ ሁለተኛ ለሚወጡ 25 ሺህ እንዲሁም ሦስተኛ ደረጃን ይዘው ለሚያጠናቅቁ 20 ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከት ታውቋል። ፌዴሬሽኑ ለአጠቃላይ የገንዘብ ሽልማት ብቻ ከ400 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የመደበ መሆኑም በመግለጫው ላይ ይፋ ሆኗል።
ይህ ውድድር በየዓመቱ የሚከናወን እና ለአገሪቱ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራት ዓይነተኛ ሚና የሚጫወት ትልቅ የውድድር ምዕራፍ መሆኑን የፌዴሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሐሪ ጠቁመዋል። በፌዴሬሽኑ የተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ከሚዲያ አካላት ለተነሱ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ከተሰጠበት በኋላ ፍጻሜውን አግኝቷል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የሴቶች ተሳትፎ ባልተረጋገጠበት የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እውን ማድረግ እንደማይቻል ተገለጸ
መጋቢት 14 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ከክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጋር በመተባበር በሚያዘጋጀው “ጉሚ በላል” የሃሳብ መድረክ... read more
ከተማ አስተዳደሩ ለ2018 በጀት ዓመት 14.5 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት መያዙን ተገለጸ
ነሐሴ 19 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኑሮ መጋራት በሚል በተለያዩ ዘርፎች ላይ በቀጥታ 14.5 ቢሊዮን ብር ድጎማ መዘጋጀቱን የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ... read more
ከሶቭየት ህብረት ዘመን የመጣው የሩሲያው ግዙፍ የሬዲዮ ቴሌስኮፕ
መስከረም 07 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በሩሲያ ምድር ውስጥ ጥልቀት ባለው ስፍራ የሚገኘው ግዙፉ ካሊያዚን አርቲ-64 (Kalyazin RT-64) የተባለ የሬዲዮ ቴሌስኮፕ፣... read more
✅ቆይታ ከኢ/ር ቢጂአይ ናይከር ጋር
♻️በፀደይ የሬዲዮ ፕሮግራም በመናኸሪያ ሬዲዮ 99.1
ዛሬ ህዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00-3፡00 ይጠብቁን!
__
ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን
መናኸሪያ ሬዲዮ 99.1
ሃሳብ፣አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት... read more
ኮንዶም ላይ ተጥሎ የነበረው የተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲነሳ መወሰኑ ተገለጸ
ኅዳር 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሃገራችን የኮንዶም አቅርቦት እጥረት መኖሩን ተከትሎ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት እየጨመረ እንዳለ ይገለጻል።
የኤች አይ... read more
የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት የመድሃኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች መመሪያ የግሉን ዘርፍ የሚያበረታታ ነው ተባለ
የመመሪያው መፅደቅ በዘርፉ የሚስተዋለውን ክፍተት ለመሸፈን አስፈላጊ እንደሆነ የገለፁት የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ መመሪያው ግንቦት... read more
ሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት በቅርቡ በቤርሙዳ ቲያትር ስራ እንደሚጀምር ተገለጸ
ኅዳር 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ከተመሰረተ 88 ዓመታትን ያስቆጠረው ሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት በ2015 ዓ.ም ጥቅምት ወር ላይ የዕድሳት መርሃ... read more
በመዲናዋ ሲካሄድ የነበረው የማህበረሰብ የጤና መድህን ምዝገባ ከተያዘው እቅድ ከ85 በመቶ በላይ መሳካቱ ተገለጸ
ታኅሳስ 01 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የጤና መድህን ምዝገባ በመዲናዋ ከጥቅምት 1 ቀን 2017 ጀምሮ ለ2 ወራት ሲከናወን መቆየቱ ይታወሳል፡፡
በህዝብ ተወካዮች... read more
የኦሮሚያ ክልል ሰሞኑን በጅማ ዞን የተከሰተውን ጉዳይ በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል
የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ ውስጥ በኢንቨስትመንት ተሰማርተው ይሰሩ በነበሩት በአቶ ዛኪር አባ ኦሊ ላይ አስደንጋጭ... read more
ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስርና እንግልት እየተዳረጉ ነው በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ገለጸ
ታኅሳስ 03 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት በሰጠው መግለጫ፤ የመገናኛ ብዙሃኑን ዘገባ ተከትሎ አደረኩት ባለው ማጣራት፣ በሀገሪቱ... read more
ምላሽ ይስጡ