ሰኔ 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)አገልግሎቱ 100 የከባድ ጭነት ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በሂደት ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ሀገሪቱ የደረሰችበትን የዕድገት ደረጃ የሚመጥን የከባድ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት ለመዘርጋት የ5 ዓመት ዕቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነም ይታወቃል፡፡
የአገልግሎቱ የማርኬቲንግ መምሪያ ኃላፊና ተወካይ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደምሰው በንቲ፤ በመርከብ፣ በከባድ ተሽከርካሪዎችና በሌሎችም ዘርፎች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ ታቅዶ በዚህ ዓመት ብቻ 100 የከባድ ተሽከርካሪዎችን በመግዛት አጠቃላይ ቁጥሩን ወደ 6 መቶ 52 ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ የወደብ ፍላጎቷን ለማሟላት በርካታ ሥራዎችን እየሠራች ባለችበት በአሁኑ ወቅት፤ ፈጣን፣ ዘመናዊና በተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮች የተሳሰሩ አሰራሮችን መዘርጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ አሁን ላይ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በሚያስችል መልኩ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎችን ለማስገባት በሂደት ላይ መሆናቸውን አቶ ደምሰው ተናግረዋል፡፡
የባህር ትራንስፖርት ዘርፉ በሰው ሀብት ማብቃት፣ በዘመናዊ አሠራርና በመሣሪያ አቅርቦት ረገድ በሚጠበቀው ልክ አይደለም ያሉት ዳይሬክተሩ፤ እነዚህን ክፍተቶች ለማሟላት የ5 ዓመት ዕቅድ ተነድፎ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠትና አሠራሩን ለማቀላጠፍ በርካታ የማሻሻያ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ድጋፍ የሚሹት በጎ አድራጎት ድርጅቶች..👉
https://youtu.be/eMP3cELi4bk
read more
ከ’ኒያ ፋውንዴሽን ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ እሌኒ ዳምጠው ጋር የተደረገ ቆይታ
https://youtu.be/mGoRJ_xcaHE
read more
ሚኒ ፓኪው ወደ ቦክሱ አለም እንደሚመለስ አሳውቋል
በ2021 የቦክስ ጓንቱን የሰቀለው አንጋፋው ቡጢኛ ማኒ ፓኪው ከስፖርቱ ራሱን አግልሎ በማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ተጠምዶ በሀገሩ ፊሊፒንስ ከ2016-22... read more
በአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ላይ የማይሳተፉ ሃገራትን በተመለከተ ህብረቱ ሃላፊነት ወስዶ ሊሰራበት እንደሚገባ ተጠቆመ
የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ በየአመቱ የህብረቱ መቀጫ በሆነችው አዲስ አበባ እንደሚካሄድ ይታወቃል፡፡
በዚህም 55 አባል ሃገራት ያሉት ህብረቱ በየአመቱ በመገናኘት የተለያዩ አህጉሩን... read more
የንግድ ተቋማት ምዝገባ እስከ ቀጣይ ዓመት ሚያዝያ ወር ድረስ እንሚጠናቀቅ ተገለጸ
ሐምሌ 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በገጠር እና በከተማ የሚገኙ መደበኛም ሆነ ኢ-መደበኛ ነጋዴዎች ፣አምራቾች እና ኢንተርፕራይዞች ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ቆጠራ እንደሚደረግ... read more
አርሰናል እና ማንችስተር ዩናይትድ በኤፍ ኤ ካፕ ይገናኛሉ
ኅዳር 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ሁለቱ የሊጉ ተወዳጅነት መንስኤዎች እንዲሁም በሀገራችን ኢትዮጵያም ሆነ በአህጉራችን አፍሪካ በርካታ ደጋፊዎች ያሏቸው ሁለቱ ክለቦች... read more
‹‹የቅድመ ማስጠንቀቂያ ክፍተቶችን በጋራ እንሙላ›› በሚል መሪ ቃል አለም አቀፍ የሜትሮዎሎጂ ቀን ተከበረ
አለም አቀፍ የሜትሮሎጂ ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ64ተኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ44ተኛ ጊዜ በዛሬው ዕለት ተከብሮ መዋሉ ተገልጻል፡፡ በአለም... read more
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከአዲሱ የኢራን መንግሥት ጋር በኒውክሌር ጉዳይ ላይ በቅርበት ለመሥራት ስምምነት ላይ መደረሱን አስታወቁ
መጋቢት 30 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ከተካሄደው "ውጤታማ የመንግሥት ለውጥ" በኋላ ከአዲሱ የሀገሪቱ አመራር ጋር... read more
ኮሚሽኑ አጀንዳ ለማሰባሰብ ወደ ሌሎች አህጉራት እና ሀገራት በሚሄድበት ጊዜ ኮሚሽኑን ለመቀበል ቅድም ዝግጅት ማድረጉን የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ገለጸ
ሐምሌ 07 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ከዚህ ቀደም ዲያስፖራው ማህበረሰብ በበየነ መረብ እና በሌሎች አማራጮች ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አጀንዳውን ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣... read more
ምላሽ ይስጡ