ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ “አካታች የባንክ አገልግሎት ለሁሉም!” በሚል መሪ ቃል፤ ከሰኔ 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ ቆይታ የሚኖረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን የማስፋት ንቅናቄ በዛሬው ዕለት አስጀምሯል።
ሁለተኛው ብሔራዊ የፋይናንስ አካታችነት ስትራቴጂ እንደሚያሳየው፣ በኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ወደ 45 በመቶ ቢያድግም፤ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎትን ሊጠቀም ይችላል ተብሎ ከሚታሰበው የኅብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሆነው 12 በመቶው ብቻ እንደሆነ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ገልጸዋል።
በሀገራችን ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኅብረተሰብ ክፍል፣ ከሃይማኖታዊ ዕሴቶቹ ጋር የሚስማማ የባንክ አገልግሎት ስላልተዘጋጀለትና ተደራሽ ስላልሆነ ከአካታች የባንክ አገልግሎት ርቆ መቆየቱን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። በተለይም የባንክ አገልግሎት ተደራሽነቱ አናሳ መሆን፣ ሴቶች ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተጠቃሚነት በእጅጉ እንዲገለሉ ማድረጉንም አብራርተዋል።
በመሆኑም መንግሥት በኢትዮጵያ የፋይናንስ አካታችነትን እና ተደራሽነትን የሚያጎለብቱ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ያሉት አቶ አቤ ሳኖ፤ ከእነዚህም አንዱ ብሔራዊ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን ለማስፋፋት የሚሠራው ሥራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ንግድ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር በአፋር፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ፣ አማራ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ፣ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ዝቅተኛ በሆነባቸው ከ241 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች እና የገጠር ቀበሌዎች የሚተገበር የንቅናቄ መርሃ ግብር ማስጀመሩን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ አምስት ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎች ስለወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ግንዛቤ የመፍጠር ዓላማን ያነገበ መሆኑም ተነግሯል።
ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ከጀመረበት ጥቅምት 2006 ዓ.ም ጀምሮ፣ በወለድ ምክንያት ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተገልለው የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ወደ መደበኛው የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲገቡ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ኢትዮ ቴሌኮም ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልገው ገለጸ
ታኅሳስ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በተያዘው በጀት ዓመት በተለያዩ ገጠራማ የሃገሪቱ ክፍሎች ለአገልግሎት ማስፋፊያ ስራ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንሚያስፈልግ... read more
የደቡብ አፍሪካ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ በእንግሊዝ መንግስት ቪዛ መከልከላቸውን ተቃወሙ
የኢኮኖሚ ፍሪደም ፋየርስ ፓርቲ መሪ ጁሊየስ ማሌማ በእንግሊዝ ሊያደርጉት የነበረው ጉብኝት በቪዛ ምክንያት ከጉዞ መታገዳቸውን መርህ አልባ ሲሉ ተችተውታል።
የምዕራባውያን ኢምፔሪያሊዝም... read more
መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ከግማሽ ሚሊዮን የሚልቁ ዜጎችን ማስተናገድ የሚችል አዲስ የገና ኤክስፖ ሊከፈት ነው ተባለ
ታኅሳስ 02 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በሮበስት ቢዝነስ ግሩፕ እና በሰላሳ መልቲ ሚዲያ አዘጋጅነት፣ ለ24 ቀናት የሚቆይ ሀገር አቀፍ ኤክስፖ ከንግድና... read more
በዲጂታል ዘርፍ ወጣቶችን ለማብቃትና ለማሰልጠን ዓላማ ያደረገው “አዶናይ ቲክቶክ አካዳሚ” ሊከፈት ነው
ሰኔ 20 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ወጣቶች በፍጥነት እየተለወጠ ያለውን የዲጂታል ዓለም በተሳካ ሁኔታ እንዲቀላቀሉና እንዲያሸንፉ ለማስቻል “አዶናይ ቲክቶክ አካዳሚ” ሥራ... read more
♻️ዘመንን በዜማ
✅በትዕግስቱ በቀለ
ድሮን ከዘንድሮ በመረጃ እና በሙዚቃ እያዋሃደ በልዩ አቀራረብ ያዝናናል፡፡
በልዩ ቅምሻ አለም እንዴት አደረች፤ዋለች እና አመሸች ሲል በትንታኔ ያስቃኘናል!
🟢ዘውትር ረቡዕ... read more
42ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብስባ ውሳኔዎች
🔰የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 42ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
1.በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ የአደጋ... read more
ከትራፊክ አደጋ እስከ አሰቃቂ የህይወት ምዕራፍ …የህክምና እጦት
እናት ለቤቷ ምሶሶ እንደሆነች ይታወቃል ልጆችም ከሌላው ቤተሰብ በተሻለ መልኩ ከእናታቸው ጋር የቀረበ ግንኙነት እንደለቸው ነው የሚነገረው፤ በሃገራችን ኢትዮጵያ ብሎም... read more
ድጋፍ የሚሹት በጎ አድራጎት ድርጅቶች..👉
https://youtu.be/eMP3cELi4bk
read more
በከባድ የሙስና ወንጀል ምርመራ የተጣራባቸው አሥራ አንድ ተጠርጣሪዎች ክስ ተመስርቶባቸዋል – የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ
ሕዳር 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በከባድ የሙስና ወንጀል ምርመራ የተጣራባቸው አሥራ አንድ ተጠርጣሪዎች ክስ እንደተመሰረተባቸው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
ክስ የተመሰረተባቸውም1ኛ ተከሳሽ... read more
በግድያ ወንጀል እና ከባድ በሰው አካል ላይ ጉዳት ማድረስ ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተቀጣ
ተከሳሽ በፍቃዱ ተሰማ በጋምቤላ ክልል በማጃንግ ብሔረሰብ ዞን በጎደሬ ወረዳ ካቦ ቀበሌ ውስጥ በቀን 22/4/2015 ዓ/ም ከምሽቱ 1 ሰዓት አካባቢ... read more
ምላሽ ይስጡ