ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ “አካታች የባንክ አገልግሎት ለሁሉም!” በሚል መሪ ቃል፤ ከሰኔ 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ ቆይታ የሚኖረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን የማስፋት ንቅናቄ በዛሬው ዕለት አስጀምሯል።
ሁለተኛው ብሔራዊ የፋይናንስ አካታችነት ስትራቴጂ እንደሚያሳየው፣ በኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ወደ 45 በመቶ ቢያድግም፤ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎትን ሊጠቀም ይችላል ተብሎ ከሚታሰበው የኅብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሆነው 12 በመቶው ብቻ እንደሆነ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ገልጸዋል።
በሀገራችን ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኅብረተሰብ ክፍል፣ ከሃይማኖታዊ ዕሴቶቹ ጋር የሚስማማ የባንክ አገልግሎት ስላልተዘጋጀለትና ተደራሽ ስላልሆነ ከአካታች የባንክ አገልግሎት ርቆ መቆየቱን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። በተለይም የባንክ አገልግሎት ተደራሽነቱ አናሳ መሆን፣ ሴቶች ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተጠቃሚነት በእጅጉ እንዲገለሉ ማድረጉንም አብራርተዋል።
በመሆኑም መንግሥት በኢትዮጵያ የፋይናንስ አካታችነትን እና ተደራሽነትን የሚያጎለብቱ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ያሉት አቶ አቤ ሳኖ፤ ከእነዚህም አንዱ ብሔራዊ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን ለማስፋፋት የሚሠራው ሥራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ንግድ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር በአፋር፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ፣ አማራ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ፣ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ዝቅተኛ በሆነባቸው ከ241 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች እና የገጠር ቀበሌዎች የሚተገበር የንቅናቄ መርሃ ግብር ማስጀመሩን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ አምስት ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎች ስለወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ግንዛቤ የመፍጠር ዓላማን ያነገበ መሆኑም ተነግሯል።
ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ከጀመረበት ጥቅምት 2006 ዓ.ም ጀምሮ፣ በወለድ ምክንያት ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተገልለው የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ወደ መደበኛው የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲገቡ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በወጣቶች ስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል ስምምነት መደረጉ ተገለጸ
የፌደራል የስነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ከኢትዮጵያ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ማህበር ጋር በስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን... read more
ሳይንቲስቶች ከጨረቃ አፈር ውኃና ኦክሲጅን በፀሐይ ብርሃን በማውጣት አዲስ ግኝት አስመዘገቡ
በጨረቃ ላይ መኖር ይቻል ይሆን?
ሐምሌ 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ሳይንቲስቶች ከጨረቃ አቧራ (regolith) ውኃና ኦክሲጅንን በፀሐይ ብርሃን ብቻ ማውጣት የሚያስችል አዲስ... read more
በጄምስ ዌብ የጠፈር ቴሌስኮፕ ሳንድ ክላውድስ ተገኘ
👉አዲሱ ግኝት በስነ ፈለክ ጥናት አለምን አስደምሟል!
ሰኔ 28 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የጄምስ ዌብ የጠፈር ቴሌስኮፕ (JWST) ባደረገው ታሪካዊ ምልከታ፣ በሩቅ... read more
የህዝብ ቁጥር ማሻቀብና የጤና ዘርፉ ተግዳሮት
https://youtu.be/fWAa-xCiJDk
read more
አዲሱ የትራፊክ ህገ ደንብና የአሽከርካሪዎች ቅሬታ
👉
https://youtu.be/8FjEsKobePo
read more
የፓርቲ አመራሮችን ለማሰልጠን የተደረሰው ስምምነት አግባብ ያለውና የፖለቲካ ምህዳሩን ሊያሻሽለው የሚችል ነው ተባለ
ኅዳር 09 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የተለያየ ሃሳብ እና አቋም ያላቸው ከ60 በላይ የሚሆኑ ሃገርና... read more
የኢትዮጵያ ፖሊስ ጥናት ኢንስቲትዩት ባለፉት 2 አመታት ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋር የተገናኘ ጥናት አላካሄድኩም አለ
ጥር 08 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ተቋማት በተለያዩ ጉዳዮች የሚያወጧቸዉን ሪፖርቶች ፖሊሲዎችን ለመፈተሽና ለፖሊሲ ግብዓትነት እየተጠቀምኩባቸዉ ነዉ ሲል የኢትዮጵያ ፖሊሰ ጥናት... read more
አሜሪካ የሱዳኑን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል በአገሪቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽሟል በሚል ከሰሰች
ጥር 01 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) አሜሪካ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽሟል ከሚለው ክስ ባለፈ የቡድኑ መሪ... read more
ምላሽ ይስጡ