ሰኔ 17 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)አገልግሎቱ 100 የከባድ ጭነት ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት በሂደት ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ሀገሪቱ የደረሰችበትን የዕድገት ደረጃ የሚመጥን የከባድ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት ለመዘርጋት የ5 ዓመት ዕቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነም ይታወቃል፡፡
የአገልግሎቱ የማርኬቲንግ መምሪያ ኃላፊና ተወካይ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደምሰው በንቲ፤ በመርከብ፣ በከባድ ተሽከርካሪዎችና በሌሎችም ዘርፎች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ ታቅዶ በዚህ ዓመት ብቻ 100 የከባድ ተሽከርካሪዎችን በመግዛት አጠቃላይ ቁጥሩን ወደ 6 መቶ 52 ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ የወደብ ፍላጎቷን ለማሟላት በርካታ ሥራዎችን እየሠራች ባለችበት በአሁኑ ወቅት፤ ፈጣን፣ ዘመናዊና በተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮች የተሳሰሩ አሰራሮችን መዘርጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ አሁን ላይ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በሚያስችል መልኩ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎችን ለማስገባት በሂደት ላይ መሆናቸውን አቶ ደምሰው ተናግረዋል፡፡
የባህር ትራንስፖርት ዘርፉ በሰው ሀብት ማብቃት፣ በዘመናዊ አሠራርና በመሣሪያ አቅርቦት ረገድ በሚጠበቀው ልክ አይደለም ያሉት ዳይሬክተሩ፤ እነዚህን ክፍተቶች ለማሟላት የ5 ዓመት ዕቅድ ተነድፎ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠትና አሠራሩን ለማቀላጠፍ በርካታ የማሻሻያ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የአካል ጉዳተኞች የስራ ስምሪት አዋጅ መኖሩን የማያውቁ ተቋማት መኖር የአካል ጉዳተኞች አካታችነት ላይ ከፍተኛ ችግር እየፈጠረ ነዉ ተባለ
በሃገራችን የአካል ጉዳተኞች የስራ ስምሪት አዋጅ ቢኖርም አሁንም የሚታየው የስራ ስምሪት የአካል ጉዳተኛ ሰራተኛውን ያማከለ አሰራር ባለመኖሩ ያለውን የግንዛቤ ክፍተት... read more
የሌሎች ሀገራት የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ለሀገራችን ኢትዮጵያ ምን ትምህርት ይሰጣሉ?
በተለያዩ ሀገራት የተከናወኑ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ለሀገራችን በጎ የሚሆን ትምህርትን አስቀምጠውልን እንዳለፉ የስነ-ምክክር መዛግብት ያስረዳሉ፡፡
የደቡብ አሜሪካዊቷ ኮሎምቢያ እ.አ.አ ከ2012-2016 ያካሄደችው... read more
ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ለትግራይ ልማት ማህበር የተሰጠ ማሳሰቢያ
ሙሉ መግለጫው ከታች ተያይዟል
ጉዳዩ፡ ማህበሩ በቅርቡ ያካሄደው ጉባኤን ይመለከታል
የትግራይ ልማት ማህበር (ትልማ) በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ቁጥር 1113/2011 መሰረት በመዝገብ... read more
ዜጎችን ለከፍተኛ ወጪና እንግልት እየዳረገ የሚገኘው እና እልባት ያልተገኘለት የአይን ህመም 👉
https://youtu.be/yz1cl1L67vo
read more
በካይሮ በቴሌኮም ሕንፃ የእሳት አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ 26 መቁሰላቸው ተሰማ
ሐምሌ 1 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በግብፅ ዋና ከተማ ካይሮ ማዕከላዊ ክፍል በሚገኝ አንድ የቴሌኮም ኢጅፕት ሕንፃ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ አራት... read more
ምክር ቤቱ ሁለት የብድር ስምምነት አዋጆችን አጽድቋል
ጥር 19 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ በዛሬው ዕለት... read more
ህፃን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በ13 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
አሳምነው ስዩም ታምራት የተባለ የ40 ዓመት እድሜ ያለው ግለሰብ 1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 627/1/፤/4/(ሀ) ላይ የተደነገገውን ህግ በመተላለፍ... read more
በክልሉ የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የምክክር ሂደት እንዳይካሄድ ለማደናቀፍ የሚሰሩ አካላት እኩይ ተግባራቸውን ቢቀጥሉም፤ ህዝቡ ጦርነትን እምቢ እንዲልና ከሰላም ፈላጊው ጎን እንዲቆም ጥሪ ቀረበ
ሐምሌ 29 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢትዮጵያ ሐገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል የሚካሄደውን የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የምክክር ሂደት እንዳያከናውን እንቅፋት ለመሆን የሚሰሩ... read more
የጤና አግልግሎት በመስጠት 25 ዓመታትን ያስቆጠረው አዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል የህክምና ጥራትን በማስጠበቅ ረገድ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
በ1992 ዓ.ም የተቋቋመው አዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል የተለያዩ የጤና አገልግሎቶችን በመስጠት 25 ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን የህክምና አሰጣጥ ጥራቱን በማሻሻል አሁን... read more
በአዲስ አባባ ከተማ ከህንጻ ተደራሽነት ጋር በተያያዘ ግልጽ የአቤቱታ ማቅረቢያ መድረክ አዘጋጅቶ መፍትሔ እያሰጠ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጸ
በመዲናዋ በህንጻ ተደራሽነት ዙሪያ ግልጽ የአቤቱታ ማቅረቢያ መድረክ ተዘጋጅቶ አካል ጉዳተኞች ለመንግስት አመራሮች ቅሬታቸውን አቅርበው ምላሽ ማግኘታቸውን ኮሚሽኑ ለጣቢያችን አስታውቋል፡፡
ኮሚሽኑ... read more
ምላሽ ይስጡ