ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ በፋይናንስ ዘርፍ ላይ ያሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ወደ አገር ውስጥ ገብተው ሥራ እንዲጀምሩ አዋጅ መዘጋጀቱን ተከትሎ፣ የአገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት እንዳይዳከሙ መጠናከር እንደሚገባቸው በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማት ለጣቢያችን ገልጸዋል።
በአገር ውስጥ ያለው የፋይናንስ አሠራር እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ አገር በቀል የሆኑ የፋይናንስ ተቋማት ማደግ በሚገባቸው ልክ እንዳያድጉ ማድረጉን የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ የኢንተርፕራይዝ ማኔጅመንት ዳይሬክተር አቶ ፍሥሐ ተስፋዬ ገልጸዋል። በአንጻሩ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ የተሰማሩ ተቋማት በጋራና በጥምረት ሊሠሩባቸው የሚችሉ ጉዳዮችን በመለየት ማጠናከር እንደሚገባቸው ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ በርካታው የማኅበረሰብ ክፍል የሚገኘው በአገሪቱ ገጠራማ አካባቢዎች ላይ እንደመሆኑ፣ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ የኅብረት ሥራ ተቋማት አቅማቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የኢንፊኒቲ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ተቋም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ እስክንድር መኩሪያ ይገልጻሉ። በተለይም ደግሞ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ የሚስተዋለው የትብብር ማነስ፣ የጥሬ ገንዘብ እጥረትና ተደራሽነት፣ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማት ጥቂት መሆን ሊሻሻሉ የሚገቡ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።
የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ዶክተር ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ወደ አገር ውስጥ ገብተው ሥራ መጀመራቸው ለትልልቅ የኢንቨስትመንት ሥራዎች እና ለውጭ ምንዛሬ አቅርቦት በጎ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ተናግረዋል። ከሰሞኑ በኢንቨስትመንት ባንክ ሥራ ላይ የተሰማራው የናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል ግሩፕ በካፒታል ገበያ ላይ ሕጋዊ ፈቃድ ያገኘ ሲሆን፣ በቀጣይም በኢትዮጵያ በባንክ አገልግሎት ዘርፍም ሆነ በኢንሹራንስ ዘርፍ የተሰማሩ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ፈቃድ አግኝተው ሥራ ሲጀምሩ ለኢኮኖሚው ጠቃሚ እንደሚሆኑና በአገር በቀል ባንኮች ላይ ጫና እንደማያሳድሩ አመላክተዋል።
የውጭ አገር ባንኮች በአገር ውስጥ ገብተው እንዲሠሩ የሚፈቅደው አዋጅ መጽደቁ የሚታወስ ሲሆን፣ የኢንሹራንስ ድርጅቶች እንዲሠሩ የሚፈቅደው ረቂቅ አዋጅም በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በትግራይ ክልል ለውሃ ማጣሪያነት የሚያገለግል ምንም አይነት ኬሚካል ባለመኖሩ እስካሁን 113 ሰው በኮሌራ ወረርሽኝ መያዙ ተገለጸ
ነሐሴ 12 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በክልሉ አሁን ላይ ለውሃ ማጣሪያነት የሚያገለግል ምንም አይነት ኬሚካል አለመኖሩንና በከፍተኛ ሁኔታ የኮሌራ ስርጭት መበራከቱን... read more
የፈተና ሂደቱን በሚያውኩ ተማሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ተገለጸ
ዘንድሮ ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8/2017 ዓ/ም የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና 608 ሺህ ተማሪዎች እንደሚወስዱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች... read more
ተቃዋሚ ፓርቲ በምርጫ ተቃውሞ ወደ 700 የሚጠጉ ሰዎች ተገድለዋል አለ
ጥቅምት 22 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በታንዛኒያ ባለፉት ሦስት ቀናት ውስጥ በምርጫው ውጤትና ሂደት ላይ በተነሳው ተቃውሞ ምክንያት በተፈጠረ ግጭት ሳቢያ፣... read more
ለአንድ ሃገር ዘላቂ ሰላም መስፈን ከሚያስፈለጉ ነገሮች መካከል በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ያለው ግንኙነት የጠነከረ እና ሰላማዊ መሆን እንዳለበት ይገለጻል፡፡
ቢሆንም ግን በሃገራችን ያለው የፖለቲካ ውቅር እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ግንኙነት ደካማ ሆኖ የቆየ መሆኑ ይነሳል።
ቢሆንም ግን ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ... read more
🚨 ሰበር ዜና፦ በሞስኮ ሰማይ ላይ የድሮን ውሽንፍር! ዩክሬን በሁለት ዓመት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ጥቃት ፈጸመች
ሰኔ 11 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ዩክሬን ላለፉት ሁለት ዓመታት ካደረገቻቸው ጥቃቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነውን የድሮን ጥቃት በሩሲያ ዋና ከተማ... read more
አፍሪካ በተባበሩት መንግስታ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ሁለት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት እንደሚገባ ተጠየቀ
በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው 38ተኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ አፍሪካ በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት እንደሚገባ ተጠይቋል።
የአፍሪካ ህብረት... read more
በዘንድሮ በጀት ዓመት ለማዳበሪያ ግዢ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር መመደቡን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ
አገልግሎቱ ይህን ያለው ትላንት ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡ ለዘንድሮ የምርት ዘመን የሚገዛው የማዳበሪያ መጠን ካለፈው ዓመት አንጻር የ4... read more
አፍሪካ በሁሉም መስክ ከተረጂነት ወጥታ ራሷን ለመቻል ጥረት ማድረግ ይገባታል ተባለ
ጥር 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)አሜሪካ ከአለም የጤና ድርጅት አባልነት እንደምትወጣ ማስታወቋን ተከትሎ ውሳኔዋ የአለምን ብሎም የአፍሪካን የጤና ችግር ሊጎዳው እንደሚችል... read more
የአጋዥ ቴክኖሎጂ አቅርቦት ፈጣን ትኩረትን እንደሚሻ ተገለፀ
በኢትዮጵያ በአሁ ወቅት አገልግሎት የሚሰጡ በርካታ የተሃድሶ ማዕከላት ቢኖሩም በቂ አለመሆናቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታወቋል።
በአሁኑ ወቅት ከ22 በላይ የተሃድሶ ማዕከላት ቢሮም... read more
የ13 ዓመት ህጻንን መንገድ ላይ ጠብቆ አስገድዶ የደፈረው ግለሠብ በፅኑ እስራት ተቀጣ
ኅዳር 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ተከሳሽ እሠየ ደባሽ የተባለ ግለሰብ በደሐና ወረዳ 014 ቀበሌ ግራር ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ በ2016 ዓ/ም የ13... read more
ምላሽ ይስጡ