ሰኔ 02 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ተግባራዊ በሆነው አዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ውስጥ የሀገር በቀል እውቀት ከጽሑፍ ያለፈ ለትግበራ የተዘጋጀ አካሄድ የለም ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ጤና መምህር እና በሀገር በቀል እውቀት ዙሪያ ምርምር የሚያደርጉት ፕሮፌሰር መንገሻ አድማሱ ለጣቢያችን ተናግረዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የተጠና ጥናት ቢኖረውም ወደ ትግበራ አልገባም የሚሉት ባለሙያው፣ ሰነድ ማዘጋጀትና መተግበር እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ሌሎች ተቋማትም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በአዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ሀገር በቀል እውቀቶችን አካቶ በትምህርት ቤቶች ውስጥ እንዲተገበር ለማስቻል የማስፈጸሚያ ሰነድ እየተዘጋጀ መሆኑን በትምህርት ሚኒስቴር የሀገር በቀል እውቀትና የማህበረሰብ ትስስር ዴስክ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላም አለሙ ለመናኸሪያ ሬዲዮ ተናግረዋል።
ፍኖተ ካርታው መተግበር ከጀመረ ዓመታትን ያስቆጠረ እንደሆነ የተናገሩት ዳይሬክተሯ፣ ነገር ግን የሀገር በቀል እውቀትን አካቶ ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ለማስቻል የሚቀሩ ስራዎች መኖራቸውን አምነዋል።
ዳይሬክተሯ በሚመሩት የሀገር በቀል እውቀትና የማህበረሰብ ትስስር ዴስክ በኩል የማስፈጸሚያ መመሪያ ሰነድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። ይህ ብቻም ሳይሆን አሁን ላይ በካሪኩለም ወይም በስርዓተ ትምህርት ክፍሉም በኩል እንዲሁ የማስፈጸሚያ መመሪያዎች መቀረጻቸውን ገልጸዋል። ስርዓተ ትምህርቱ ሙሉ በሙሉ የሀገር በቀል እውቀትን እንዲያካትት ለማስቻል ነው በቂ ቅድመ ዝግጅት ያስፈለገው ሲሉም አክለው ተናግረዋል።
አዲስ የትምህርት ፍኖተ ካርታ መቅረጽ ያስፈለገው ሀገር በቀል እውቀቶችን ለማካተት እንደሆነ ካሁን ቀደም የትምህርት ሚኒስትሩ መናገራቸው ይታወሳል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ለአማራ ክልል ከ5 ሚሊየን ብር በላይ የሚሆን የምግብ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ
ታኅሳስ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል በተከሰተው ድርቅ የከፋ ችግር ላይ ለሚገኙ ዜጎች ከ5 ሚሊዮን ብር... read more
ሶማሊያ ለብሔራዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን በይፋ ልታስጀምር መሆኑ ተገለጸ
ሃገሪቱ እ.ኤ.አ ከ1967 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ አገራዊ ቀጥተኛ ምርጫ ለማከናወን እየተዘጋጀች ነው ተብሏል።
ሶማሊያ እሁድ በዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ ብሔራዊ የመራጮች ምዝገባ... read more
ከዛሬ ጀምሮ ከ13 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ህፃናት የፖሊዮ ክትባት ሊሰጥ ነው ተባለ
ህፃናት ላይ የሚከሰተውን ፖሊዮ እና ተጓዳኝ በሽታዎችን ለመከላከል በዘመቻ መልክ የፖሊዮ ክትባት ሊሰጥ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለመናኸሪያ... read more
ከሬሳ ሳጥን የተሰማው አስደንግጭ ማንኳኳት፡ ሞተዋል ተብለው በስህተት የተቀበሩት አያት አስገራሚ ታሪክ!
ሐምሌ 30 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ኢኳዶር፣ ባባሆዮ በተባለች ከተማ የሚገኘው ማርቲን ኢካዛ ሆስፒታል ሰኔ 9 ቀን 2015... read more
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ምስል ያረፈበት የ24 ካራት ወርቅ ሳንቲም ሊታተም ነው
መጋቢት 15 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአሜሪካ የነፃነት 250ኛ ዓመት መታሰቢያን አስመልክቶ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ምስል ያለበት ባለ 24 ካራት የወርቅ ሳንቲም... read more
ኢሰመኮ ለአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚቀርብላቸው ድጋፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱን ቢገለጽም ቅሬታዎች አልደረሱኝም ሲል የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ
ኅዳር 17 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ለአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚቀርብላቸው ድጋፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ በመጠንም ሆነ... read more
የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ 1.5 ሚሊየን የሚጠጉ ጎብኚዎች ወደ ላሊበላ ከተማ ያቀናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገለጸ
ታኅሳስ 19 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በዚህ ባለንበት ወርሃ ታህሳስ መጨረሻ ላይ የሚከበረዉን የገና በዓል በስፋት ከሚከበርባቸው ቦታዎች መካከል አንዱ የላሊበላ... read more
በከተማዋ የሚገኙ ተማሪዎች የሰሯቸውን የሳይንስ እና የፈጠራ ውጤቶች ወደ ተግባር ለመቀየር በትኩረት ይሰራል ተባለ
በመጠናቀቅ ላይ በሚገኘው የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን፣ በከታማዋ ያሉ ተማሪዎች ስራ ላይ ሊውሉ የሚችሉ በርካታ የሳይንስ እና የፈጠራ ውጤቶችን ማቅረባቸውን... read more
አፍሪካ አቅም ግንባታ ፋውንዴሽን በ33 ዓመታት ጉዞው የአህጉሪቱን የልማት አቅም በማጎልበት ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል ተባለ
መስከረም 27 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የአፍሪካ አቅም ግንባታ ፋውንዴሽን (Africa Capacity Building Foundation - ACBF) ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ለ33 ዓመታት... read more
የአጋዥ ቴክኖሎጂ አቅርቦት ፈጣን ትኩረትን እንደሚሻ ተገለፀ
በኢትዮጵያ በአሁ ወቅት አገልግሎት የሚሰጡ በርካታ የተሃድሶ ማዕከላት ቢኖሩም በቂ አለመሆናቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታወቋል።
በአሁኑ ወቅት ከ22 በላይ የተሃድሶ ማዕከላት ቢሮም... read more
ምላሽ ይስጡ