ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ሊቨርፑል በዚህ ክረምት የተከላካይ መስመሩን ማጠናከር ዋነኛ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ አድርጎ ወደ ዝውውር ገበያው ለመግባት መዘጋጀቱ ተዘግቧል። በክለቡ የግራ ተከላካይ መስመር ላይ ሚሎስ ኬርኬዝ እና ኮስታስ ሲሚካስ በመኖራቸው ቦታው አስተማማኝ ቢሆንም፤ በመሀል ተከላካይ ክፍል ግን ያለው አማራጭ አናሳ ሆኗል። በተለይም የኢብራሂማ ኮናቴ ክለቡን ለቆ መውጣት፣ እንዲሁም የቪርጅል ቫን ዳይክ እና ጆ ጎሜዝ ውል ወደ መጨረሻው ዓመት መግባቱ ሊቨርፑልን ልምድ ላላቸው ተከላካዮች እጥረት ዳርጎታል። ምንም እንኳን ክለቡ ወጣቱን ጄርሚ ዣኬን ከሬኔ ማስፈረም ቢችልም፣ እንዲሁም ጆቫኒ ሌኦኒ ከከባድ የጉልበት ጉዳት ቢያገግምም፤ ሊቨርፑል ለረጅም እና ለአጭር ጊዜ የሚጠቅመውን አስተማማኝ ተከላካይ ለማግኘት የኮከቦችን ዝርዝር አዘጋጅቷል።
ሊቨርፑል በዝርዝሩ ቀዳሚ ያደረገው በአውሮፓ በስፋት ከሚፈለጉ ተከላካዮች አንዱ የሆነውን የስፖርቲንግ ሊዝበኑን ጎንካሎ ኢናሲዮን ነው። ክለቡ ኳስን ከኋላ መስርቶ ወደ ፊት ማሳለፍ የሚችል እና የግራ እግር ተጫዋች የሆነ ተከላካይ የሚፈልግ ሲሆን፤ ይህ የ24 ዓመቱ ተጫዋች ለቫን ዳይክ ምርጥ አጋዥ ይሆናል ተብሎ ይታመናል። ለስፖርቲንግ ከ250 በላይ ጨዋታዎችን ማድረግ የቻለውና ለፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ቋሚ ተሰላፊ መሆን የቻለው ኢናሲዮ፣ በውሉ ላይ የ52 ሚሊዮን ፓውንድ ማፍረሻ ያለው በመሆኑ ለሊቨርፑል ተመጣጣኝ የገንዘብ አማራጭ ሊሆን ይችላል።
ምንም እንኳን ማንቸስተር ዩናይትድ እና ቼልሲ ተጫዋቹን ቀደም ብለው ቢፈልጉትም፣ ሊቨርፑል ግን የኮናቴን ምትክ በአስቸኳይ ስለሚፈልግ ተጫዋቹን ለማግኘት የተሻለ ዕድል አለው ተብሏል። ከኢናሲዮ በተጨማሪ የናፖሊው ሳም ቢውኬማ፣ የቶተንሃሙ ወጣት ሉካ ቩስኮቪች እና የኖቲንግሃም ፎረስቱ ሙሪሎ በሊቨርፑል የዝውውር ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ክለቡ የተከላካይ መስመሩን የወደፊት ዕድል ለመገንባት በሚቀጥሉት ሳምንታት ጠንካራ እንቅስቃሴ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የውጊያ ጄት በትምህርት ቤት ውስጥ ተከስክሶ ቢያንስ 19 ተማሪዎች ሲሞቱ ከ50 በላይ የሚሆኑት መቁሰላቸው ተገለጸ
👉የብሔራዊ ሃዘን ቀን ታውጇልም ተብሏል
ሐምሌ 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በባንግላዲሽ ዋና ከተማ ዳካ በሚገኝ አንድ የኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ የባንግላዲሽ አየር... read more
ከደረሰኝ ጋር የተገናኙ ጠቅላላ ወንጀሎች
👉ማንኛውም ደረሰኝ የመስጠት ግዴታ ያለበት ታክስ ከፋይ ያለደረሰኝ ግብይት ያከናወነ እንደሆነ ከብር 25ሺ (ሃያ አምስት ሺ ብር) እስከ ብር 50... read more
አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት የንግድ ጦርነትን በ15 በመቶ ታሪፍ እንዲሆን ተስማሙ
ሐምሌ 21 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ህብረት ለረዥም ጊዜ ሲያስጨንቅ የነበረውን የንግድ ጦርነት ለማስቀረት የሚያስችል ታሪፍ ስምምነት... read more
ለሙት አንሳ ገዳም የገቢ ማሰባሰብ ዘመቻ 30 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡ ተገለጸ
መስከረም 14 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር፣ ምስራቅ በለሳ ወረዳ የሚገኘው የሙት አንሳ ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መነኮሳትን... read more
እግሯን በእንቅስቃሴ ላይ ሳለች በተቀበረ ቦምብ ያጣችው ዝሆን ሰው ሠራሽ እግር ተገጠመላት
መስከረም 07 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) በታይላንድ የምትገኘው ሞሻ የተባለችው እስያዊት ዝሆን፣ ገና በህፃንነቷ እንቅስቃሴ ላይ በነበረችበት ጊዜ በተቀበረ ቦምብ... read more
በከተማዋ 19 መስመሮች እስከ ምሽት 4 ሰዓት በቋሚነት የአውቶቢስ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ
ታኅሳስ 21 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ የአውቶቢስ ትራንስፖርት አገልግሎት ከሚሰጡ መስመሮች 19ኙ በቋሚነት እስከ ምሽት 4፡00 ሰዓት አገልግሎት... read more
በበቆጂ አቅራቢያ በሚገኘው የጋለማ ደን የተነሳዉን እሳት ለማጥፋት መሳሪያ ቢጠየቅም ማግኘት አልተቻለም ተባለ
ለአንድ ሳምንት ያህል በአርሲ የሚገኘው የጋለማ ደን በእሳት ውስጥ እንደሚገኝ ያስታወቀው የአርሲ ተራራሮች ብሄራዊ ፓርክ ነው፡፡
መናኸሪያ ሬዲዮ ያነጋገራቸው የፓርኩ ሃላፊ... read more
የሀሳብ እና የጤና ውህደት የሚፈጥሩት ሃይል….
https://youtu.be/OiX1D87jowU
read more
ኮሚሽኑ አጀንዳ ለማሰባሰብ ወደ ሌሎች አህጉራት እና ሀገራት በሚሄድበት ጊዜ ኮሚሽኑን ለመቀበል ቅድም ዝግጅት ማድረጉን የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ገለጸ
ሐምሌ 07 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ከዚህ ቀደም ዲያስፖራው ማህበረሰብ በበየነ መረብ እና በሌሎች አማራጮች ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አጀንዳውን ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣... read more
♻️የፕሮግራም ማስታወሻ
ቅዳሜ ጥር 01 ቀን 2017 ዓ.ም በመናኸሪያ እንግዳ ፕሮግራማችን የወጋገን ባንክ ፕሬዝደንት አክሊሉ ወበት ዶ/ር እንግዳችን በመሆን የህይወት ተሞክሮና ልምዳቸውን... read more
ምላሽ ይስጡ