ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ሊቨርፑል በዚህ ክረምት የተከላካይ መስመሩን ማጠናከር ዋነኛ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ አድርጎ ወደ ዝውውር ገበያው ለመግባት መዘጋጀቱ ተዘግቧል። በክለቡ የግራ ተከላካይ መስመር ላይ ሚሎስ ኬርኬዝ እና ኮስታስ ሲሚካስ በመኖራቸው ቦታው አስተማማኝ ቢሆንም፤ በመሀል ተከላካይ ክፍል ግን ያለው አማራጭ አናሳ ሆኗል። በተለይም የኢብራሂማ ኮናቴ ክለቡን ለቆ መውጣት፣ እንዲሁም የቪርጅል ቫን ዳይክ እና ጆ ጎሜዝ ውል ወደ መጨረሻው ዓመት መግባቱ ሊቨርፑልን ልምድ ላላቸው ተከላካዮች እጥረት ዳርጎታል። ምንም እንኳን ክለቡ ወጣቱን ጄርሚ ዣኬን ከሬኔ ማስፈረም ቢችልም፣ እንዲሁም ጆቫኒ ሌኦኒ ከከባድ የጉልበት ጉዳት ቢያገግምም፤ ሊቨርፑል ለረጅም እና ለአጭር ጊዜ የሚጠቅመውን አስተማማኝ ተከላካይ ለማግኘት የኮከቦችን ዝርዝር አዘጋጅቷል።
ሊቨርፑል በዝርዝሩ ቀዳሚ ያደረገው በአውሮፓ በስፋት ከሚፈለጉ ተከላካዮች አንዱ የሆነውን የስፖርቲንግ ሊዝበኑን ጎንካሎ ኢናሲዮን ነው። ክለቡ ኳስን ከኋላ መስርቶ ወደ ፊት ማሳለፍ የሚችል እና የግራ እግር ተጫዋች የሆነ ተከላካይ የሚፈልግ ሲሆን፤ ይህ የ24 ዓመቱ ተጫዋች ለቫን ዳይክ ምርጥ አጋዥ ይሆናል ተብሎ ይታመናል። ለስፖርቲንግ ከ250 በላይ ጨዋታዎችን ማድረግ የቻለውና ለፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ቋሚ ተሰላፊ መሆን የቻለው ኢናሲዮ፣ በውሉ ላይ የ52 ሚሊዮን ፓውንድ ማፍረሻ ያለው በመሆኑ ለሊቨርፑል ተመጣጣኝ የገንዘብ አማራጭ ሊሆን ይችላል።
ምንም እንኳን ማንቸስተር ዩናይትድ እና ቼልሲ ተጫዋቹን ቀደም ብለው ቢፈልጉትም፣ ሊቨርፑል ግን የኮናቴን ምትክ በአስቸኳይ ስለሚፈልግ ተጫዋቹን ለማግኘት የተሻለ ዕድል አለው ተብሏል። ከኢናሲዮ በተጨማሪ የናፖሊው ሳም ቢውኬማ፣ የቶተንሃሙ ወጣት ሉካ ቩስኮቪች እና የኖቲንግሃም ፎረስቱ ሙሪሎ በሊቨርፑል የዝውውር ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ክለቡ የተከላካይ መስመሩን የወደፊት ዕድል ለመገንባት በሚቀጥሉት ሳምንታት ጠንካራ እንቅስቃሴ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በአደገኛ ጦር ተወግታ የ100 አመት እድሜ ያስቆጠረች ዓሣ ነባሪ
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአላስካ አዳኞች በተያዘችው ዓሣ ነባሪ ላይ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የተሰራ የጦር ጫፍ መገኘቱ ሳይንቲስቶችን አስገርሟል።
ይህ... read more
የአፍሪካ ወጣቶች እጣ-ፋንታ
አፍሪካ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ሃብቶች የታደለች ምቹ መልካ ምድርና ከፍተኛ ቀጥር ያለው ትኩስ የሰው ኃይል ቢኖራትም በሠላም እጦት ምክንያት አፍሪካ... read more
የአጋዥ ቴክኖሎጂ አቅርቦት ፈጣን ትኩረትን እንደሚሻ ተገለፀ
በኢትዮጵያ በአሁ ወቅት አገልግሎት የሚሰጡ በርካታ የተሃድሶ ማዕከላት ቢኖሩም በቂ አለመሆናቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታወቋል።
በአሁኑ ወቅት ከ22 በላይ የተሃድሶ ማዕከላት ቢሮም... read more
የኢትዮጵያ ሚዲያ ዳሰሳ፡ በነፃነት፣ በኢኮኖሚ እና በፀጥታ ተግዳሮቶች መካከል
ሙሉ ዘገባውን ለመስማት ሊንኩን ይጫኑ
በተጠናቀቀው የበጀት አመት መገናኛ ብዙሃን መረጃ ለህዝቡ በተለያዩ አማራጮች ከማሻገር ባለፈ የነበራቸው አዎንታዊ እና አሉታዊ ሚና... read more
ከውጭ እርዳታ ጥገኝነት ለመላቀቅ የመከረው የምስራቅ አፍሪካ የበጎ አድራጎት ጉባኤ በአዲስ አበባ ተጠናቀቀ
ሰኔ 12 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ከ30 በላይ ሀገራትን የወከሉ ከ600 በላይ ተሳታፊዎች የተገኙበት 10ኛው የምስራቅ አፍሪካ የበጎ አድራጎት ጉባኤ ከውጭ... read more
ባለፉት አራት ወራት ውስጥ 420 ሚሊየን ዶላር የውጪ ምንዛሬ ለባንኮች ተሽጧል ተባለ
ሐምሌ 08 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ብሄራዊ ባንክ ከመጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ጀመሮ በየሁለት ሳምንት ሲያካሂደ የነበረው የውጪ ምንዛሬ ጨረታ... read more
በሃዋሳ ጅቦች በቀን የሚጎበኙበት ሥፍራ በመዘጋጀቱ ተጨማሪ የቱሪስት መዳረሻ እየሆነ እንደሚገኝ ተገለጸ
በሃረሪ ክልል በስፋት ጅቦችን በማላመድ ለቱሪስት የማስጎብኘት እንቅስቃሴ በቱሪዝም ዘርፉ የሚታወቅ ነው።በልዩ ሁኔታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሃዋሳም ጅቦች በቀን የሚጎበኙበትን... read more
በሱዳን አዲስ የኮሌራ ወረርሽኝ በመከሰቱ በአንድ ሳምንት ውስጥ 172 ሰዎች ሞቱ
በሱዳን በተከሰተው አዲስ የኮሌራ ወረርሽኝ ባለፈው ሳምንት 172 ሰዎች ሲሞቱ ከ2,500 በላይ የሚሆኑት በቫይረሱ መያዛቸውን የሀገሪቷ ባለስልጣናት አስታውቀዋል፡፡
በሱዳን ዋና ከተማ... read more
እስራኤልና ኢራን ሶስተኛ ቀናቸውን ቀጥለውበታል
እስራኤል እና ኢራን ለሶስተኛ ተከታታይ ቀን ጥቃቶችን እየተለዋወጡ ሲሆን፣ ሁለቱም ሀገራት ለአጥቂነት ምላሽ መስጠታቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ይህ ውጥረት ከዚህ ቀደም... read more
የአሜሪካው ደግ ዳኛ በ88 አመታቸው ማረፋቸውን ተከትሎ የመንግስት ባንዲራዎች በግማሽ እንዲውለበለቡ ትዕዛዝ ተሰጠ
ነሐሴ 15 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በፍርድ ቤት ባሳዩት ርህራሄና ቀልድ የተሞላበት ባህሪያቸው “የአሜሪካ ደግ ዳኛ” በመባል በዓለም ዙሪያ የሚታወቁት ተወዳጁ... read more
ምላሽ ይስጡ