ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ሊቨርፑል በዚህ ክረምት የተከላካይ መስመሩን ማጠናከር ዋነኛ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ አድርጎ ወደ ዝውውር ገበያው ለመግባት መዘጋጀቱ ተዘግቧል። በክለቡ የግራ ተከላካይ መስመር ላይ ሚሎስ ኬርኬዝ እና ኮስታስ ሲሚካስ በመኖራቸው ቦታው አስተማማኝ ቢሆንም፤ በመሀል ተከላካይ ክፍል ግን ያለው አማራጭ አናሳ ሆኗል። በተለይም የኢብራሂማ ኮናቴ ክለቡን ለቆ መውጣት፣ እንዲሁም የቪርጅል ቫን ዳይክ እና ጆ ጎሜዝ ውል ወደ መጨረሻው ዓመት መግባቱ ሊቨርፑልን ልምድ ላላቸው ተከላካዮች እጥረት ዳርጎታል። ምንም እንኳን ክለቡ ወጣቱን ጄርሚ ዣኬን ከሬኔ ማስፈረም ቢችልም፣ እንዲሁም ጆቫኒ ሌኦኒ ከከባድ የጉልበት ጉዳት ቢያገግምም፤ ሊቨርፑል ለረጅም እና ለአጭር ጊዜ የሚጠቅመውን አስተማማኝ ተከላካይ ለማግኘት የኮከቦችን ዝርዝር አዘጋጅቷል።
ሊቨርፑል በዝርዝሩ ቀዳሚ ያደረገው በአውሮፓ በስፋት ከሚፈለጉ ተከላካዮች አንዱ የሆነውን የስፖርቲንግ ሊዝበኑን ጎንካሎ ኢናሲዮን ነው። ክለቡ ኳስን ከኋላ መስርቶ ወደ ፊት ማሳለፍ የሚችል እና የግራ እግር ተጫዋች የሆነ ተከላካይ የሚፈልግ ሲሆን፤ ይህ የ24 ዓመቱ ተጫዋች ለቫን ዳይክ ምርጥ አጋዥ ይሆናል ተብሎ ይታመናል። ለስፖርቲንግ ከ250 በላይ ጨዋታዎችን ማድረግ የቻለውና ለፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ቋሚ ተሰላፊ መሆን የቻለው ኢናሲዮ፣ በውሉ ላይ የ52 ሚሊዮን ፓውንድ ማፍረሻ ያለው በመሆኑ ለሊቨርፑል ተመጣጣኝ የገንዘብ አማራጭ ሊሆን ይችላል።
ምንም እንኳን ማንቸስተር ዩናይትድ እና ቼልሲ ተጫዋቹን ቀደም ብለው ቢፈልጉትም፣ ሊቨርፑል ግን የኮናቴን ምትክ በአስቸኳይ ስለሚፈልግ ተጫዋቹን ለማግኘት የተሻለ ዕድል አለው ተብሏል። ከኢናሲዮ በተጨማሪ የናፖሊው ሳም ቢውኬማ፣ የቶተንሃሙ ወጣት ሉካ ቩስኮቪች እና የኖቲንግሃም ፎረስቱ ሙሪሎ በሊቨርፑል የዝውውር ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ክለቡ የተከላካይ መስመሩን የወደፊት ዕድል ለመገንባት በሚቀጥሉት ሳምንታት ጠንካራ እንቅስቃሴ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በማይናማር የሚገኙ ዜጎችን ማስመለሱ ቢቀጥልም አሁንም በህገ ወጥ መንገድ ወደ ስፍራው የሚያቀኑ ዜጎች መበራከታቸው ተገልጿል
በማይናማር የሚገኙ ዜጎችን ማስመለሱ ቢቀጥልም አሁንም በህገ ወጥ መንገድ ወደ ስፍራው የሚያቀኑ ዜጎች መበራከታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ... read more
ትላንት የተጠናቀቀው የፈረንጆቹ 2024 በአፍሪካ ሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱበት ዓመት ነበር ተባለ
ታኅሳስ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) እ.ኤ.አ 2024 በአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የስደተኞች አደጋ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ እንዲሁም የታጣቂዎች ግጭት ከፍተኛ... read more
ከ66ሺሕ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች ስልጠና ወስደው ወደ ማህበረሰቡ መቀላቀላቸው ተገለጸ
ነሐሴ 08 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ካሉ የታጣቂ ቡድኖች ሰላም ፈልገው እጅ የሰጡ ግለሰቦችን ወደ ብሄራዊ የታሃድሶ... read more
ኢትዮቴሌኮም በ2018 በጀት ዓመት 235 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አስታወቀ
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው በጀት አመት 162 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ማስታወቁ ይታወሳል።
በ2018 በጀት አመት በገጠርና... read more
ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ጉዳይ ከውጪ ሃገራት ጋር የምታደርገውን ግንኙነት በጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ብልሃት መምራት እንደሚገባት ተገለጸ
መጋቢት 17 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በቀይ ባህር ጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረቱ እየጨመረ በመምጣቱ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟን ለማስከበር በምትከተለው መርህ የቀጠናው ውስብስብ የፖለቲካ... read more
ለሙት አንሳ ገዳም የገቢ ማሰባሰብ ዘመቻ 30 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡ ተገለጸ
መስከረም 14 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር፣ ምስራቅ በለሳ ወረዳ የሚገኘው የሙት አንሳ ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መነኮሳትን... read more
በሰባ ቦሩ ወረዳ በአፈር መደርመስ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል
በጉጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች በአፈር መደርመስ አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡
አደጋው ትናንት... read more
በከተማዋ የሚገኙ ተማሪዎች የሰሯቸውን የሳይንስ እና የፈጠራ ውጤቶች ወደ ተግባር ለመቀየር በትኩረት ይሰራል ተባለ
በመጠናቀቅ ላይ በሚገኘው የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን፣ በከታማዋ ያሉ ተማሪዎች ስራ ላይ ሊውሉ የሚችሉ በርካታ የሳይንስ እና የፈጠራ ውጤቶችን ማቅረባቸውን... read more
ፕሬዝደንት ትራምፕ የፌዴራል ሪዘርቭ ገዢ የሆኑትን ሊሳ ኩክን ‘በሞርጌጅ ማጭበርበር’ ወንጀል ከስልጣናቸው አነሱ
ነሐሴ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የፌዴራል ሪዘርቭ ባንክ ገዢ የሆኑትን ሊሳ ኩክን በሞርጌጅ ማጭበርበር ወንጀል... read more
በክልሎች ያለው የኢትዮ-ቴሌኮም አገልግሎት ተደራሽነት ሊፈተሸ እንደሚገባ ተጠቆመ
ታኅሳስ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በሃገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የቴሌኮም አግልግሎት ተደራሽነት አሁን ክፍተቶች የሚስተዋልበት መሆኑን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት... read more
ምላሽ ይስጡ