ግንቦት 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በፋርስ ባህረ ሰላጤ አካባቢ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተቀሰቀሰው ወታደራዊ ግጭት በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱን ተከትሎ፣ የኢራን የጦር ኃይሎች በኩዌት እና በባህሬን የሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋማትን ኢላማ ያደረገ ሰፊ የሚሳይል እና የድሮን ጥቃት ሰንዝረዋል። በዚህ ጥቃት ሳቢያ በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በደረሰ ፍንዳታ የአንድ ንጹህ ዜጋ ሕይወት ሲያልፍ፣ በደርዘን የሚቆጠሩ መቁሰላቸው ተረጋግጧል። ክስተቱን ተከትሎ ኩዌት እና ባህሬን የኢራንን ድርጊት በፅኑ አውግዘዋል።
የኩዌት መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄነራል ሳውድ አብዱልአዚዝ አል-ኦታይቢ በሰጡት መግለጫ፣ ረቡዕ ዕለት መንፈቅ ሌሊት ላይ በርካታ ቁጥር ያላቸው የጠላት ድሮኖች የኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ተርሚናል 1 (Terminal 1) ንዑስ ክፍል መምታታቸውን ይፋ አድርገዋል። ጥቃቱ በአውሮፕላን ማረፊያው ሲቪል መሠረተ ልማት ላይ ከፍተኛ የቁስ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ በወቅቱ በአካባቢው የነበሩ በርካታ ሰዎችን አቁስሏል።
የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ባወጣው መረጃ መሰረት በጥቃቱ የአንድ ህንዳዊ ዜጋ ሕይወት ወዲያውኑ ያለፈ ሲሆን፣ ከፍተኛ የጭንቅላት እና የፍንዳታ አደጋ የደረሰባቸውን ጨምሮ 63 ሰዎች የአደጋ ጊዜ ቀዶ ጥገና እና የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል። አደጋውን ተከትሎ የንግድ በረራዎች በሙሉ ተቋርጠው የነበረ ቢሆንም፣ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ከሌሎች ተርሚናሎች በከፊል መጀመራቸው ተገልጿል።
የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ምክር ቤት (IRGC) በበኩሉ ጥቃቱን በይፋ የሰነዘረ መሆኑን ባይክድም፣ ኢላማው የሲቪል አውሮፕላን ማረፊያ ሳይሆን በኩዌት የሚገኘው አሊ አል ሳሌም የአሜሪካ አየር ማዕከል (Ali Al Salem Air Base) እና በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ 5ኛ የባህር ኃይል እዝ መሆኑን አስታውቋል። የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳለው ከሆነ፣ ይህ ጥቃት የተሰነዘረው አሜሪካ በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ በምትገኘው የኢራኗ ቀሽም ደሴት (Qeshm Island) ላይ ላደረሰችው የድሮን መቆጣጠሪያ ጣቢያ ጥቃት እና በአንድ የነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ለፈጸመችው የሚሳይል ድብደባ የተሰጠ ቀጥተኛ የአጸፋ ምላሽ ነው። ኢራን አክላም የኩዌት እና የባህሬን መንግሥታት ግዛቶቻቸውን አሜሪካ በኢራን ላይ ወታደራዊ ጥቃት እንድትሰነዝርበት በመፍቀዳቸው ለተፈጠረው ጥፋት ቀጥተኛ ኃላፊነት አለባቸው ስትል ወንጅላለች።
በአካባቢው የሚገኘው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) በበኩሉ፣ ኢራን ወደ ኩዌት እና ባህሬን የላከቻቸውን ከ30 በላይ ባሊስቲክ ሚሳይሎች እና ባለአንድ አቅጣጫ ተወርዋሪ ድሮኖች (Kamikaze drones) የአሜሪካ እና የባህሬን የአየር መከላከያ ሥርዓቶች ማክሸፍ መቻላቸውን ገልጿል። ይሁን እንጂ የኩዌት ጦር ኃይሎች በሰጡት መረጃ፣ አንዳንድ የሚሳይል ስብርባሪዎች እና ድሮኖች በመኖሪያ መንደሮች እና በሲቪል ተቋማት ላይ ማረፋቸውን አረጋግጠዋል።
ይህ የቅርብ ጊዜ እርስ በርስ የመጠቃቃት እርምጃ፣ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ባለፈው ሚያዝያ ወር ተደርሶ የነበረውን ተሰባሪ የተኩስ አቁም ስምምነት ለአደጋ ያጋለጠ ሲሆን፣ በፋርስ ባህረ ሰላጤው የነዳጅ ማጓጓዣ መስመር ላይ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ስጋት ፈጥሯል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ወንዶች በዓመት 7 ሰዓት በመታጠቢያ ቤት ውስጥ ያሳልፋሉ ተባለ
ነሐሴ 08 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) አዲስ የተደረገ ጥናት እንደሚያመለክተው፣ ወንዶች በዓመት በአማካይ ሰባት ሰዓታትን የሚጠቀሙት በመታጠቢያ ቤት ውስጥ ነው፤... read more
የክልሉ መንግስት ለ9 መቶ 90 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ9 መቶ 90 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ።
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ መጪውን የትንሳኤ... read more
በግብዓት እጥረት ምክንያት የማምረት አቅሙ በግማሽ መቀነሱን የሰበታ አግሮ ኢንዱስትሪ ገለጸ
በቀን ከ150 ሺህ ሊትር በላይ ወተት እና የወተት ተዋፅኦ የማቀነባበር አቅም ያለው የሰበታ አግሮ ኢንዱስትሪ፣ በግብዓት እጥረት ምክንያት እስካሁን በቀን... read more
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ ጥያቄ ተጠቃሚ ለመሆን በርካታ የቤት ስራዎች ይጠብቋታል ተባለ
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ ለማግኘት በምታደርገው እንቅስቃሴ በኩል ተጠቃሚ ለመሆን በርካታ የዲፕሎማሲ ስራዎች ይጠበቁባታል ሲሉ ለመናኸሪያ... read more
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተሰሩ ስራዎች ወደሃገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶች በሃገር ውስጥ በመተካት ከ2.8 ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
ጥር 01 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በተለያዩ ዘርፎች ላይ ሙሉ በሙሉ እና በከፊል ከውጪ በሚገቡ ምርቶች በሃገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎች በመሸፈናቸው ከዚህ... read more
ወቅቱ የወባ ትንኝ መፈልፈያ ቢሆንም እንደ ሃገር ያለው የወባ ስርጭት መጠን መሻሻል የታየበት ነው ተባለ
ጥቅምት 06 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)ከመስከረም እስከ ታህሳስ ያለው ወቅት የወባ ትንኝ የሚፈለፈልበት መሆኑን ተከትሎ በተቀናጀ ሁኔታ በየሳምንቱ በየክልሎች ያለውን ፤የመገምገም... read more
ኮሚሽኑ ለጠቅላላ ጉባኤው የአመካካሪዎች ሥልጠና መስጠት ጀመረ
ሰኔ 11 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በዛሬው ዕለት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አመካካሪዎች ሁለተኛ ዙር ሥልጠናን በአዲስ አበባ... read more
በቀሪዎቹ የክረምት ወራት ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደሚኖር ተገለጸ
ነሐሴ 01 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ ባለፉት ሁለት የክረምት ወራት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ መደበኛና ከመደበኛ በላይ የሆነ... read more
በከተማዋ አዳዲስ የሚገነቡ ትምህርት ቤቶች፣ የልዩ ፍላጎት ተማሪዎችን ታሳቢ ባዳረገ መልኩ እንደሚሰሩ ተገለጸ
በአዲስ አበባ ከተማ አዳዲስ በሚገነቡ ትምህርት ቤቶች፣ በሁሉም ዘርፍ የልዩ ፍላጎት ወይም ስፔሻል ኒድ ተማሪዎችን ታሳቢ ተደርገው እንደሚገነቡ የከተማ አስተዳደሩ... read more
ሃምሳ በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ጭነት በባቡር ለማጓጓዝ እየተሰራ ነው- የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር
መጋቢት 13 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በየአመቱ የማጓጓዝ አቅሙን እያሳደገ የመጣው የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አ.ማ ሃምሳ በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ጭነት... read more
ምላሽ ይስጡ