ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ “አካታች የባንክ አገልግሎት ለሁሉም!” በሚል መሪ ቃል፤ ከሰኔ 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ ቆይታ የሚኖረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን የማስፋት ንቅናቄ በዛሬው ዕለት አስጀምሯል።
ሁለተኛው ብሔራዊ የፋይናንስ አካታችነት ስትራቴጂ እንደሚያሳየው፣ በኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ወደ 45 በመቶ ቢያድግም፤ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎትን ሊጠቀም ይችላል ተብሎ ከሚታሰበው የኅብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሆነው 12 በመቶው ብቻ እንደሆነ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ገልጸዋል።
በሀገራችን ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኅብረተሰብ ክፍል፣ ከሃይማኖታዊ ዕሴቶቹ ጋር የሚስማማ የባንክ አገልግሎት ስላልተዘጋጀለትና ተደራሽ ስላልሆነ ከአካታች የባንክ አገልግሎት ርቆ መቆየቱን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። በተለይም የባንክ አገልግሎት ተደራሽነቱ አናሳ መሆን፣ ሴቶች ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተጠቃሚነት በእጅጉ እንዲገለሉ ማድረጉንም አብራርተዋል።
በመሆኑም መንግሥት በኢትዮጵያ የፋይናንስ አካታችነትን እና ተደራሽነትን የሚያጎለብቱ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ያሉት አቶ አቤ ሳኖ፤ ከእነዚህም አንዱ ብሔራዊ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን ለማስፋፋት የሚሠራው ሥራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ንግድ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር በአፋር፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ፣ አማራ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ፣ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ዝቅተኛ በሆነባቸው ከ241 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች እና የገጠር ቀበሌዎች የሚተገበር የንቅናቄ መርሃ ግብር ማስጀመሩን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ አምስት ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎች ስለወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ግንዛቤ የመፍጠር ዓላማን ያነገበ መሆኑም ተነግሯል።
ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ከጀመረበት ጥቅምት 2006 ዓ.ም ጀምሮ፣ በወለድ ምክንያት ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተገልለው የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ወደ መደበኛው የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲገቡ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
በዓለም የመጀመሪያው የተሳካ የብልት ንቅለ ተከላ
👉በዓለም የመጀመሪያው የተሳካ የብልት ንቅለ ተከላ ከተደረገ ከስድስት ወራት በኋላ አንድ ጤናማ ሕፃን መወለዱ ተዘግቧል
ሐምሌ 22 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በደቡብ... read more
ሁለተኛው ዙር የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ ፌዴሬሽን የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር እየተከናወነ ይገኛል
የ2017ዓ.ም ሁለተኛው ዙር የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ ፌዴሬሽን የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ እየተከናወነ ይገኛል።
በውድድሩ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ... read more
የዓለም ረጅሙን የሥራ ዘመን ያስመዘገቡት የ100 ዓመቱ አዛውንት ክብረ ወሰን ሰበሩ
ነሐሴ 27 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ዋልተር ኦርትማን የተባሉ ብራዚላዊ አዛውንት በአንድ ኩባንያ ውስጥ ለረጅም ጊዜ በመሥራት የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት... read more
የርህራሄ ትምህርት የምትሰጠው ዴንማርክ
ነሐሴ 13 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ዴንማርክ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዜጎቿ ደስታ የምትታወቅ ሀገር ስትሆን፣ ይህ ስኬት ከልጅነት ጀምሮ በሚሰጡ ልዩ ትምህርቶች... read more
የባለሶስት እግር ተሽከርካሪ ባለንብረቶች የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ መሆናቸውን ካላረጋገጡ መስራት እንደማይችሉ ተገለጸ
ኅዳር 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ከዚህ ቀደም ባለንብረቶች ከተለያዩ ክልሎች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ቀድመው ይጠቀሙበት በነበረው የሰሌዳ ቁጥር ይሰሩ... read more
የኢትዮጵያ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናት በሚቀጥሉት 4 ወራት እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ
በተያዘው አመት መስከረም ወር ላይ የተጀመረው የስነ-ህዝብና ጤና ቆጠራ ባለፉት 8 ወራት ውስጥ በሁሉም የሃገሪቱ ክልሎች በተሰራው ስራ ከግማሽ በላይ... read more
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እየተከተለው ያለው ጠበቅ ያለ አሰራር ፓርቲዎችን ለቀጣዩ ምርጫ የሚያጠናክር ነው ተባለ
እግዱ የተጣለባቸው ፓርቲዎች ግን ውሳኔው ተገቢነት እና ህጋዊ መሰረት የሌለው ነው ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያዊያን እንደ አገር በቅርቡ ከሚጠብቋቸው ትልልቅ ብሔራዊ ጉዳዮች መካከል... read more
ሩሲያ ዋትስአፕን ልታግደው እየሞከረች ነው ተባለ
ነሐሴ 08 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) ዋትስአፕ (WhatsApp) የተሰኘው የመልዕክት መላላኪያ መተግበሪያ ሩሲያ አገልግሎቱን ለማገድ እየሞከረች መሆኑን አስታውቋል። ኩባንያው እንደገለጸው፣... read more
አርሰናል ከሪያል ማድሪድ የጨዋታ ዳሰሳ
አለም በጉጉት እየጠበቀው የሚገኘው የሁለቱ ቡድኖች ተጠባቂ ጨዋታ ማክሰኞ ምሽት ይከናወናል።
ሻምፒዮኖቹ ሪያል ማድሪዶች ክብራቸውን ለማስጠበቅ በወሳኝ ምዕራፍ ፤ እና አጓጊ... read more
በትውልድ ግንባታ ሂደት ወጣቶች የአርበኞችን ታሪክ እንዲረዱ ማድረግ ይገባል ተባለ
በቀደምት ጊዜ ሃገር በጠላት እጅ እንዳትወድቅ ለመከላከል በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ አርበኞች ከፍተኛ መስዋት የከፈሉበትን ቀን ለመዘከር የአርበኞች ቀን በዛሬው ዕለት... read more
ምላሽ ይስጡ