ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ “አካታች የባንክ አገልግሎት ለሁሉም!” በሚል መሪ ቃል፤ ከሰኔ 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ ቆይታ የሚኖረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን የማስፋት ንቅናቄ በዛሬው ዕለት አስጀምሯል።
ሁለተኛው ብሔራዊ የፋይናንስ አካታችነት ስትራቴጂ እንደሚያሳየው፣ በኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ወደ 45 በመቶ ቢያድግም፤ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎትን ሊጠቀም ይችላል ተብሎ ከሚታሰበው የኅብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሆነው 12 በመቶው ብቻ እንደሆነ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ገልጸዋል።
በሀገራችን ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኅብረተሰብ ክፍል፣ ከሃይማኖታዊ ዕሴቶቹ ጋር የሚስማማ የባንክ አገልግሎት ስላልተዘጋጀለትና ተደራሽ ስላልሆነ ከአካታች የባንክ አገልግሎት ርቆ መቆየቱን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። በተለይም የባንክ አገልግሎት ተደራሽነቱ አናሳ መሆን፣ ሴቶች ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተጠቃሚነት በእጅጉ እንዲገለሉ ማድረጉንም አብራርተዋል።
በመሆኑም መንግሥት በኢትዮጵያ የፋይናንስ አካታችነትን እና ተደራሽነትን የሚያጎለብቱ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ያሉት አቶ አቤ ሳኖ፤ ከእነዚህም አንዱ ብሔራዊ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን ለማስፋፋት የሚሠራው ሥራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ንግድ ባንክ ከFSD Ethiopia ጋር በመተባበር በአፋር፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ፣ አማራ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ፣ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት ዝቅተኛ በሆነባቸው ከ241 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች እና የገጠር ቀበሌዎች የሚተገበር የንቅናቄ መርሃ ግብር ማስጀመሩን ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ አምስት ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎች ስለወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ግንዛቤ የመፍጠር ዓላማን ያነገበ መሆኑም ተነግሯል።
ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ከጀመረበት ጥቅምት 2006 ዓ.ም ጀምሮ፣ በወለድ ምክንያት ከፋይናንስ ሥርዓቱ ተገልለው የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ወደ መደበኛው የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲገቡ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ክሪፕቶ ከረንሲን በኢትዮጵያ መተግበር የሚቻልበት ሁኔታ እንዳለ ተገለጸ
ታኅሳስ 12 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ከወረቀት እና የሳንቲም ገንዘብ በተጨማሪ የዲጂታል ገንዘቦች የክፍያና ኢንቨስትመንት አማራጭ እየሆኑ እንዳሉ ይገለፃል፡፡
ሀገራት ከእነዚህ መገበያያ... read more
ደረጃ የወጣላቸው ምርቶች ብሔራዊ የደረጃ ምልክት መጠቀም እንዳለባቸው ተገለጸ
አስገዳጅ ደረጃ የወጣላቸው ሁሉም ምርቶች ብሔራዊ የደረጃ ምልክት መጠቀም እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
የኢንስቲትዩቱ የሕዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ ብሩክ ሀብቴ... read more
ሃምሳ በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ጭነት በባቡር ለማጓጓዝ እየተሰራ ነው- የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር
መጋቢት 13 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)በየአመቱ የማጓጓዝ አቅሙን እያሳደገ የመጣው የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አ.ማ ሃምሳ በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ጭነት... read more
በትግራይ ክልል በተካሄደው የ8ተኛ ክልል አቀፍ ፈተና ይሳተፋሉ ተብሎ ከተጠበቀው 50 በመቶ የሚሆኑት አለመሳተፋቸው ተገለጸ
ታኅሳስ 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል በጦርነት ምክንያት ተማሪዎች በመደበኛ የትምህርት ሰዓት እየተማሩ አለመሆኑ እና የፈተና ሰዓትም ጠብቀዉ እየተፈተኑ... read more
ፊንላንድ የሐሰት ዜናን መለየትን ከ6 ዓመት ጀምሮ ማስተማር ጀመረች
👉በትምህርት ስርዓቱ አካታለች ነው የተባለው።
ነሐሴ 12 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ) በሰፊው የሐሰት መረጃ መስፋፋት በፈጠረው የዲጂታል ዘመን፣ ፊንላንድ የሐሰት መረጃዎችንና... read more
በቢሾፍቱ ከተማ 10 ሚሊዮን የሚጠጉ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ
መስከረም 21 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ በመጪው እሁድ ለሚከበረው የሆራ አርሰዲ በዓል ወደ ከተማዋ የሚያቀኑ 10 ሚሊየን የሚጠጉ... read more
ኢጋድ የአንካራውን ስምምነት እንደሚደግፍ ገለጸ
ታኅሳስ 03 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መንግስት መካከል የተደረሰውን ስምምነት እንደሚደግፍ አስታወቀ።
ስምምነቱን... read more
በ2019 በጀት ዓመት በአንድ በመቶ የተቋማት ድጋፍ ከ6 ሺህ በላይ ሕፃናትን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዷል ተባለ
ነሐሴ 08 ቀን 2018 (መናኸሪያ ሬዲዮ) በመዲናዋ ድጋፍ እና እንክብካቤ የሚያስፈልጋቸው ሕፃናት ቁጥር እየጨመረ እንደሆነ በተደጋጋሚ ይገለፃል። እነዚህን ሕፃናት ለመርዳት... read more
85ኛዉ የአገዉ የፈረሰኞች ማህበር ዓመታዊ በዓል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ
የአገው ፈረሰኞች ማህበር ዓመታዊ በዓል ከ4 ሺህ 500 በላይ ፈረሰኞች እና ከ500 በላይ እግረኞች እንዲሁም የክብር እንግዶች በተገኙበት ዘንድሮ ለ85ኛ... read more
የአድዋ ገድልን በዲፕሎማሲያዊው መስክ መጠቀም እንደሚገባ ተገለጸ
ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደረጃ ያላት እውቅና የጨመረው እና የአውሮፓ ሀያላን ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር በእኩልነት መንፈስ መደራደራቸውን የቀጠሉት ከአድዋ ማግስት መሆኑ... read more
ምላሽ ይስጡ