ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል አጀንዳ ለማሰባሰብ ክልሉን ወክለው ከሚንቀሳቀሱ ተቋማት ጋር ተደጋጋሚ ውይይት ቢደረግም፣ እስካሁን የሚፈለገው ውጤት እንዳልመጣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል።
በክልሉ አስተማማኝ እና የተረጋጋ ሰላም ባለመኖሩ ምክንያት፣ እስካሁን በቦታው በአካል ተገኝቶ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ ማከናወን እንዳልተቻለ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ተናግረዋል።
ኮሚሽኑ ሂደቱን ስኬታማ ለማድረግ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ከሕወሃት አመራር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማኅበራት፣ ከጋዜጠኞች እና ይመለከታቸዋል ከተባሉ ሌሎች ተቋማት ጋር ከ22 ጊዜ በላይ ተደጋጋሚ ውይይቶችን ቢያደርግም፤ እስካሁን ድረስ ወደ ተግባር መግባት የሚያስችል ውጤት አልተገኘም ብለዋል።
በዚህም ምክንያት ኮሚሽኑ የመጨረሻ አማራጭን በመጠቀም፣ በአዲስ አበባ ከተማ ከትግራይ ተወላጆች ጋር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ ማከናወኑን ፕሮፌሰሩ አስታውሰዋል።
በውይይቱ ላይም በቀጥታ ከትግራይ ክልል የመጡ 300 ተሳታፊዎች እና በአዲስ አበባ የሚኖሩ 400 የክልሉ ተወላጆች በጥቅሉ 700 ሰዎች መሳተፋቸውን ዋና ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ፣ ሁሉንም አካላት ያካተተ ሀገራዊ ምክክር ለማድረግ በትግራይ ክልል ያለውን ተሳትፎ ለማረጋገጥ ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱንም የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ አስታውቀዋል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በበጀት አመቱ ወደ 50 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ዋጋ የሚያወጣ መድሃኒት ማስወገዱ ተገለጸ
ሰኔ 12 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በባለስልጣኑ የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ገልገሎ ኦልጂራ፤ እንደ አገር የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው እና... read more
‘‘በደብረጽዮን የሚመራው ህወሓት ከኤርትራ መንግስት ጋር እየሰራ ነው’’ – ጊዜያዊ አስተዳደሩ
የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራር ከሆኑት ከአቶ #ጣዕመ #አረዶም ጋር የተደረገ ቆይታ
https://youtu.be/F1ilWPpFztU
read more
ወረቀትን ከሣር ማምረት ተጀመረ
መስከረም 21 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ወረቀትን ለማምረት ዛፎችን መቁረጥን የሚተካ አዲስ የዘላቂነት ፈጠራ ይፋ ተደርጓል። ተመራማሪዎች ሣርን ዋና ጥሬ እቃ... read more
በጎርፍ አደጋ ቢያንስ ስድስት ሰዎች መሞታቸው ተዘግቧል
ሰኔ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)በቻይና ጉይዙ ግዛት ባደረሰው ከባድ ጎርፍ ቢያንስ ስድስት ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ። ጎርፉ ወደ ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ... read more
3 ሺህ 400 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተገለጸ
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 3 ሺህ 400 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተገለጸ።
በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 9 ዙር በረራ... read more
የ5ሜጋ ባይት ሃርድ ድራይቭ በ1956 በአይቢኤም ሲጓጓዝ የሚያሳየው ምስል ቅርምትን ፈጥሯል
ሐምሌ 20 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ዛሬ በኪሳችን ከምንይዛቸው ጥቃቅን የኮምፒዩተር ማከማቻ መሳሪያዎች ጋር ሲነጻጸር፣ ከ60 ዓመታት በፊት የነበረው ቴክኖሎጂ ምን... read more
“የማይበገረው የማር አዳኝ”፤ የንቦችን ጥቃት የሚቋቋመው እንስሳ
ታህሳስ 14 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በዱር እንስሳት ዓለም ውስጥ እጅግ ደፋር እንደሆነ የሚነገርለት ሜርካ (Honey Badger)፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የንቦችን መንጋ... read more
ለ57ሺህ ታዳጊ ወጣቶች የክረምት የስፖርት ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ
ሰኔ 28 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ለ57ሺህ ታዳጊ ወጣቶች የክረምት የስፖርት ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን የአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ለመናኸሪያ ሬዲዮ... read more
የቴኳንዶ ስፖርት በበጀት ችግር ምክንያት የታሰበውን ያህል እያደገ አለመሆኑ ተገለጸ
እንደ ሀገር ህብረተሰቡ እንዲሁም ስፖርቱን ከመንግስት በተጨማሪ ይደግፋሉ ተብለዉ የሚታሰቡ ባለሀብቶች ስለ ቴኳንዶ ስፖርት ግንዛቤው ስለሌላቸው ተደጋጋሚ የበጀት እጥረት እንዲገጥመው... read more
ምላሽ ይስጡ