ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል አጀንዳ ለማሰባሰብ ክልሉን ወክለው ከሚንቀሳቀሱ ተቋማት ጋር ተደጋጋሚ ውይይት ቢደረግም፣ እስካሁን የሚፈለገው ውጤት እንዳልመጣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል።
በክልሉ አስተማማኝ እና የተረጋጋ ሰላም ባለመኖሩ ምክንያት፣ እስካሁን በቦታው በአካል ተገኝቶ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ ማከናወን እንዳልተቻለ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ተናግረዋል።
ኮሚሽኑ ሂደቱን ስኬታማ ለማድረግ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ከሕወሃት አመራር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማኅበራት፣ ከጋዜጠኞች እና ይመለከታቸዋል ከተባሉ ሌሎች ተቋማት ጋር ከ22 ጊዜ በላይ ተደጋጋሚ ውይይቶችን ቢያደርግም፤ እስካሁን ድረስ ወደ ተግባር መግባት የሚያስችል ውጤት አልተገኘም ብለዋል።
በዚህም ምክንያት ኮሚሽኑ የመጨረሻ አማራጭን በመጠቀም፣ በአዲስ አበባ ከተማ ከትግራይ ተወላጆች ጋር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ ማከናወኑን ፕሮፌሰሩ አስታውሰዋል።
በውይይቱ ላይም በቀጥታ ከትግራይ ክልል የመጡ 300 ተሳታፊዎች እና በአዲስ አበባ የሚኖሩ 400 የክልሉ ተወላጆች በጥቅሉ 700 ሰዎች መሳተፋቸውን ዋና ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ፣ ሁሉንም አካላት ያካተተ ሀገራዊ ምክክር ለማድረግ በትግራይ ክልል ያለውን ተሳትፎ ለማረጋገጥ ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱንም የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ አስታውቀዋል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
ለ57ሺህ ታዳጊ ወጣቶች የክረምት የስፖርት ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ
ሰኔ 28 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ለ57ሺህ ታዳጊ ወጣቶች የክረምት የስፖርት ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን የአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ለመናኸሪያ ሬዲዮ... read more
ያለ ረዳት በሚሰሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ቢሆንም አሁንም ክፍተቱ እንዳለ ነው ተባለ
ሐምሌ 04 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ "ሚኒባስ" ታክሲዎች ያለ ረዳት መንቀሳቀስ እንደማይችሉ እና ተሳፋሪን... read more
በከተማዋ የሚገኙ ተማሪዎች የሰሯቸውን የሳይንስ እና የፈጠራ ውጤቶች ወደ ተግባር ለመቀየር በትኩረት ይሰራል ተባለ
በመጠናቀቅ ላይ በሚገኘው የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን፣ በከታማዋ ያሉ ተማሪዎች ስራ ላይ ሊውሉ የሚችሉ በርካታ የሳይንስ እና የፈጠራ ውጤቶችን ማቅረባቸውን... read more
ከአዲስ አበባ የሚነሱ 4 አዳዲስ የፍጥነት መንገዶች ሊገነቡ መሆኑ ታውቋል
ከአዲስ አበባ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚወጡ አራት አዳዲስ የፍጥነት መንገዶችን ለመገንባት ጥናት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታውቋል፡፡
♻️ከአዲስ አበባ... read more
ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እያለ የሚጠራው ቡድን በምክክሩ እየተሳተፉ መሆኑ ተገለጸ
ታኅሳስ 14 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የዜጎችን ሰላም ለማስፈን በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ምክክር አስፈላጊ መሆኑን በኦሮሚያ ክልል የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ... read more
የዩኤንኤድስ (UNAIDS) ሪፖርትና በአፍሪካ ሴቶች ላይ ያለው አደጋ
የተባበሩት መንግሥታት የኤድስ መከላከል ፕሮግራም (ዩኤንኤድስ) ዓለም አቀፍ የኤድስ ቀንን አስመልክቶ ይፋ ባደረገው የ2025 ሪፖርት፣ በኤድስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከ2010... read more
በኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን መካከል ለሚገነባው የመንገድ ፕሮጀክት የሚሳተፉ ስራ ተቋራጮችን የተመለከተ መስፈርት መዘጋጀቱ ተገለጸ
ኅዳር 16 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በቅርቡ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የ738 ነጥብ 2 ሚሊየን ዶላር ብድር መፍቀዷ እና በገንዘቡም በሁለቱ ሃገራት... read more
የተፋሰሱ ሃገራት ኮሚሽን ሊቋቋም ባለበት ወቅት ግብጽ ወደ ናይል ትብብር መመለሷን ኢትዮጵያ በአጽዕኖት መከታተል አለባት ተባለ
የአባይ ውሃን በፍትሀዊነት እና በምክንያታዊነት ለመጠቀም ከ15 ዓመት በፊት የተቋቋመ የናይል ቤዚ ኢንሼቲቭ ህጋዊ ቢሆንም ግብፅ ውድቅ ማድረጓዋ እና የናይል... read more
የህዝብ ቁጥር ማሻቀብና የጤና ዘርፉ ተግዳሮት
https://youtu.be/fWAa-xCiJDk
read more
ምክር ቤቱ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የሦስት ዓመት የስራ አፈፃፀምን እያዳመጠ ይገኛል
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ባካሄደው 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሦስት ዓመት የስራ... read more
ምላሽ ይስጡ