ሰኔ 03 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል አጀንዳ ለማሰባሰብ ክልሉን ወክለው ከሚንቀሳቀሱ ተቋማት ጋር ተደጋጋሚ ውይይት ቢደረግም፣ እስካሁን የሚፈለገው ውጤት እንዳልመጣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል።
በክልሉ አስተማማኝ እና የተረጋጋ ሰላም ባለመኖሩ ምክንያት፣ እስካሁን በቦታው በአካል ተገኝቶ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ ማከናወን እንዳልተቻለ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ተናግረዋል።
ኮሚሽኑ ሂደቱን ስኬታማ ለማድረግ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ከሕወሃት አመራር፣ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማኅበራት፣ ከጋዜጠኞች እና ይመለከታቸዋል ከተባሉ ሌሎች ተቋማት ጋር ከ22 ጊዜ በላይ ተደጋጋሚ ውይይቶችን ቢያደርግም፤ እስካሁን ድረስ ወደ ተግባር መግባት የሚያስችል ውጤት አልተገኘም ብለዋል።
በዚህም ምክንያት ኮሚሽኑ የመጨረሻ አማራጭን በመጠቀም፣ በአዲስ አበባ ከተማ ከትግራይ ተወላጆች ጋር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ ማከናወኑን ፕሮፌሰሩ አስታውሰዋል።
በውይይቱ ላይም በቀጥታ ከትግራይ ክልል የመጡ 300 ተሳታፊዎች እና በአዲስ አበባ የሚኖሩ 400 የክልሉ ተወላጆች በጥቅሉ 700 ሰዎች መሳተፋቸውን ዋና ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ፣ ሁሉንም አካላት ያካተተ ሀገራዊ ምክክር ለማድረግ በትግራይ ክልል ያለውን ተሳትፎ ለማረጋገጥ ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱንም የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ አስታውቀዋል።
__
ሀሳብ እና’ሳ’ፍራለን
Related Posts
የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ለእስራኤል የሚሰጠውን የ3.3 ቢሊዮን ዶላር ወታደራዊ ዕርዳታ ለማገድ በቀረበው ታሪካዊ የውሳኔ ሐሳብ ላይ ሊመክር ነው
ሰኔ 18 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ)የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ለእስራኤል የሚሰጠውን የ3.3 ቢሊዮን ዶላር ወታደራዊ ዕርዳታ ሙሉ በሙሉ ለማገድ በቀረበው አዲስ... read more
“የቆዳ ባንክ/ልገሳ በኢትዮጵያ መጀመር አለባት”የቃጠሎ ህክምናን ባለሙያዎች
ሰብዓዊ ፍጡር የሆነው የሰው ልጅ በተፈጥሮው በርካታ ድንቅ ስጦታዎች ተሰጥተውታል። ከእነዚህም መካከል ትልቁና የመጀመሪያው የሰውነት አካል የሆነው ቆዳው ነው።
የሰውነት ቆዳ... read more
የጃባን ሺንካንሰን የተሰኘው የባቡር አገልግሎት ከ60 ዓመት በላይ ምንም አይነት አደጋ አድርሶ አያውቅም ተባለ
ነሐሴ 11 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በጃፓን የሚገኘው “ሺንካንሰን” የተሰኘው ፈጣን ባቡር አገልግሎት ከ60 ዓመታት በላይ ባስቆጠረው ታሪኩ አንድም ገዳይ አደጋ... read more
መናኸሪያ #ሞግዚት
🔰ቅሬታ ያስነሱት የመዲናዋ ማሳጅ ቤቶች
በመዲኗ አሁን አሁን የማሳጅ አገልግሎት እንሰጣለን የሚሉ ማስታወቂያዎች ነዋሪዎች በስፋት በሚኖሩባቸው አከባቢዎች ላይ ሳይቀሩ መመልከት እየተለመደ... read more
በትግራይ ክልል 1 ሚሊየን የሚገመቱ ተፈናቃዮች አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ተገለጸ
ከዓመታት በፊት በነበረው የሰሜኑ ጦርነት ተፈናቅለው ወደ ቀድሞ ቀዬአቸው ያልተመለሱ ዜጎች ቁጥር በርካታ መሆኑን እና በዘላቂነት ማቋቋም እንዳልተቻለ ተገልጿል፡፡
ከፕሪቶሪያው የሰላም... read more
ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ
ጥር 06 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሹመትን አስመልክቶ የቀረበለትን የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ... read more
ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ አገራት እንደ ማዕድን ያሉ የተፈጥሮ ሀብቶች ስለምን የግጭት የስዕበት ማእከል ሆኑ? በአስተዳደር እና የህግ ማዕቀፍ ችግር ወይስ የተፈጥሮ ሀብቱ በባህሪው ግጭትን ሳቢ ስለሆነ?
አፍሪካ እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ቢኖራትም ሀብቱን ለልማት አውሎ የዜጎችን ሕይወት መቀየር፤ አህጉሪቱንም ከድህነት ማውጣት ግን አለመቻሉን የአህጉሪቱን ጉዳይን በቅርበት የሚከታተሉ... read more
በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ጊዳሚ ወረዳ ዜጎች ከጸጥታ ችግር ባለፈ በህክምና ግብዓት አቅርቦት እጥረት ምክንያት የከፋ ቀውስ ውስጥ ናቸው ተባለ
ባለፉት 5 ዓመታት በአገራችን የተለያዩ አከባቢዎች በሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮች ምክንያት የበርካቶች ህይወት ማለፉ፤ ንብረት መውደሙ እና የበዙትም ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን... read more
በኦሮሚያ ክልል የተጀመረው የሠላም ንግግር በሌሎች አካባቢዎችም ሊስፋፋ ይገባል ተባለ
ኅዳር 27 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በኦሮሚያ ክልል የተጀመሩ የሠላም ንግግሮች በሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎችም ተግባራዊ መሆን እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡ የስነ አመራር መምህር... read more
መሉጌታ ከበደን (ወሎዬው) የሚዘክር ኮሚቴ ተቋቋመ
ሐምሌ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የቀድሞ የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአጥቂ መስመር ተጫዋች የሆነው ሙሉጌታ ከበደን የሚዘክር ኮሚቴ በዛሬው... read more
ምላሽ ይስጡ